Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Friday, March 29, 2013

ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪካ የኢሕአዴግን ስብሰባ በተኑ፤ ቴዎድሮስ አድሃኖም ተደብቀው አመለጡ



ዘ-ሐበሻ) በደቡብ አፍሪካ ሮዝባንክ ከተማ የተጠራው የኢሕ አዴግ ሥብሰባ በኢትዮጵያውያን ብርቱ ትግል መቋረጡንና መበተኑን የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ሪፖርተር ከሥፍራው ዘገበ። በልማት ስም የተጠራውና በውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የተጠራው ይኸው ስብሰባ የስር ዓቱ ደጋፊ የሆኑ ከ20 የማይበልጡ ሰዎች ቢገኙም ስብሰባው ይደረግበት የነበረውን ሃያት ሆቴል የስር ዓቱ ተቃዋሚዎች በመሙላት ስብሰባው እንዳይደረግ አድርገዋል።

የድምጻችን ይሰማ፣ የኦነግ፣ የግንቦት ሰባት እና የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ አባላትና ደጋፊዎች በአንድነት የኢሕ አዴግን ስብሰባ እንዳይደረግ በማድረግ
- ከልማት በፊት የሕዝብ ነፃነት ይቅደም
- በቅድሚያ መገደብ ያለበት ወንዝ ሳይሆን የ ኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ነው በሚል ሕዝቡ ጩኸቱን በማሰማቱ ስብሰባው ተቋርጦ ደጋፊው ሕዝቡ ጥቃት ያደርስባቸዋል በሚል ፍራቻ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን ደብቆ ከአዳራሹ አስመልጧል።

የኢሕአዴግ ስብሰባ እንዳይደረግ ያስተጓጎሉት ኢትዮጵያውያን ኢሕ አዴግ በከፈለበት የሃያት ሆቴል አድራሽ ስብሰባ በማድረግ በቀጣይ በአንድነት ስለሚያደርጉት የጋራ ትግል ዙሪያ መነጋገራቸውን፤ የተዘጋጀውን ውሃ እና መጠጥም የኛ ገንዘብ ነው በሚል እንደጠጡት የዘገበው የዘሐበሻ ሪፖርተር የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሃያት ሆቴል ስብሰባው ከተስተጓጎለበት በኋላ ደጋፊዎቹን በኢምባሲው ውስጥ መሰብሰቡ ታውቋል። ከኢትዮጵያ ኢምባሲ 60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው ከሮዝባንክ ከተማም ኢትዮጵያውያን ወደ ኢምባሲው በመሄድ ተቃውሟቸውን እንዳሰሙም ሪፖርተራችን ጨምሮ ዘገቧል። zehabesha.com

ODF, a democratic alternative for Ethiopia

Lencoo Lataa(OPride) After an intense week of discussions in Minneapolis, Minnesota, the activist group Oromo Dialogue Forum on Thursday announced the formation a new political party, the Oromo Democratic Front.
This came after a year long deliberations on the direction of the Oromo people’s struggle in Ethiopia, a series of media interviews, and meetings across continents.

Leenco Lata, an intellectual and founder of the Oromo Liberation Front (OLF), a rebel group formed in 1973 by Oromo nationalists to fight for the self-determination of the Oromo people, was elected the chairman of the new organization.

OLF has fought a low key guerrilla warfare against three successive Ethiopian regimes, including the current one. But its influence waned in recent years as the organization battled numerous internal splits amid a dwindling support from the Oromo diaspora. Please read the whole from http://www.opride.com/oromsis/news/horn-of-africa/3650-breaking-news-it-s-the-oromo-democratic-front

Thursday, March 28, 2013

የመሰብሰብና የሰላማዊ ሰልፍ መብቶች

የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቶች ኢትዮጵያ ዉስጥ አለመከበራቸዉን አመለከተ።

የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በምህፃሩ ሰመጉ ባወጣዉ አንድ መቶ ሃያ አራተኛ ልዩ መግለጫ በሀገሪቱ የተለያዩ  የፖለቲካና የሲቪክ ማህበራት ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸዉ መጣሱን አጣርቶ ማሥረጃ ማካተቱን ገልጿል። ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር የሰመጉን ዳይሬክተር አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር  ዝርዝሩን ለማድመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ

ዕውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው?



የኢትዮጵያ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽ ኮሚቴና ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በመሆን ያዘጋጁት ሰላማዊ ሰልፍ አላማ ለፋሺስቱና ለጦር ወንጀለኛው ግራዚያኒ በጣሊያን ሀገር የተገነባውን መናፈሻ ስፍራና ሀውልት ለመቃወም ነው፡፡ ይህ ግለሰብ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ታሪክ አይዘነጋውም፡፡

ግራዚያኒ በመርዝ ጋዝ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ጨፍጭፏል፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ ለቀናት በዘለቀው የበቀል ጭፍጨፋም በአካፋ ሳይቀር በአዲስ አበባና በአካባቢዋ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በግፍ ጨፍጭፏል፡፡ ግራዚያኒ በወቅቱ በሰጠው ትዕዛዝ የፋሺስት ወታደሮች ህይወት ያለውን ተንቀሳቃሽ ፍጥረትን ሁሉ ገድለዋል፡፡ ይህ እሩቅ በማይባል ጊዜ የተፈፀመ ድርጊት ነው፡፡

የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለእንዲህ አይነቱ ጨፍጫፊ የተገነባን ሀውልት ለመቃወም በወጡ ዜጎች ላይ የወሰዱት የእስር ተግባር እውን ኢትዮጵያን የሚመሯት ኢትዮጵያውያን ናቸው? አስብሎናል፡፡ ኢህአዴግ በስልጣን ዘመኑ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ በተደጋጋሚ ጥፋት ፈፅሟል፡፡ ሀገራችንን የባህር በር ማሳጣትን ጨምሮ ሀገራዊ ስሜትን አንኳሶ ጠባብ የብሔር ስሜት እንዲንሰራፋ አድርጓል፣ ታሪክን ለስልጣኑ መደላድል ሲል በራሱ መንገድ የሚያዘጋጀው የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያን ጠፍጥፎ እንደሰራት ሁሉ ደርግን ለመጣል ካደረገው ትግል ውጪ ያለውን የአርበኞች ተጋድሎ እውቅና ሲሰጥ አይታይም፡፡


መንግስት ለፋሽስቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ የተገነባውን ሀውልት በመቃወም የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ሳያንስ ግራዚያኒን ለማውገዝ የወጡ ዜጎችን በመደብደብና በማንገላታት ማሰሩ አሳፍሮናል፡፡ ለዜጎቻቸው እና ለሚመሯት ሀገር ክብር የማይሰጡ ይልቁንም የጦር ወንጀለኛና ፋሺስትን ለመቃወም የወጣን ዜጋ ማሰርራቸው የኢህአዴግ ባለስልጣናት ወገንተኝነታቸው ለዜጎቻቸው ነው ወይስ ለፋሺስት? የሚል ዘግናኝ ጥያቄ እንድንሰነዝር ያስገድደናል፡፡


በሰልፉ ላይ የተገኙት ሀገር ወዳድ ዜጎች በማን አለብኝነት ሲታሰሩ ድባደባ ተፈፅሞባቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የታሳሪዎቹን የኢሜይልና የማህበራዊ ገፅ የይለፍ ቃል (password) በግዳጅ የሚቀበሉ የደህንነት ሀይሎች ተልከውባቸዋል፡፡ ይህን ቅጥ ያጣ አንባገነናዊ ድርጊት የፈፀመው ወይም እንዲፈፀም ትዕዛዝ የሰጠው አካል ማንነት ተጣርቶ የማስተካከያ እርምጃ ሊወሰድ ይገባዋል፡፡ በየምክንያቱ ዜጎችን ማሰር የለመደው አንባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ምን ያክል ኢትዮጵያዊነትን እየተዋጋ እንዳለም የሚያሳይ ድርጊት ነው፡፡ መሰረቱ ዜጎች በማንኛውም ጉዳይ ላይ የተቃውሞም ሆነ የድጋፍ ሰልፍ ማድረግ እንደሚችሉ ህገመንግስቱ ደንግጓል፡፡ ይህን መብት ዜጎች እንዳይጠቀሙ ያፈነው መንግስት፣ ኢህአዴግን የሚደግፉ አልያም በራሱ ከተጠሩ ሰልፎች ውጪ ዜጎች እንዳይሳተፉ በአሰራር ከልክሏል፡፡ ይህ የመብት ረገጣ ከመሆኑም በላይ በዜጎች መካከል 1ኛ ደረጃና 2ኛ ደረጃ ዜግነትን ያስቀመጠ ነው፡፡


የኢህአዴግን ባናውቅም፣ እኛ ኢትዮጵያውያን በቅኝ ገዢዎች የተዋረደ ስነልቦና የለንም፡፡ ሆኖም የግል ጥቅማቸውን ለማደላደል ሲሉ ለቅኝ ገዢ ጠላቶቻችን ያደሩ ባንዳዎች እንደነበሩ ታሪክ በጥቁር መዝገቡ ሸክፎታል፡፡ ይህን አሳፋሪ ተግባር በጣሊያን ወረራ ወቅት የፈፀሙ ኢትዮጵያውያን ለልጅ ልጆቻቸው የሚያስተላልፉት አንገት ቀና የሚያደርግ ታሪክ አይኖርም፡፡


በዚህም ዘመን ተመሳሳይ ክህደት የሚፈፅሙ አካላት መኖራቸው አይጠረጠርም፡፡
የኢህአዴግ መንግስት በይፋ ለጦር ወንጀለኛውና ለፋሺሽቱ ሩዶልፍ ግራዚያኒ የተሰራውን ሀውልት በይፋ ካለማውገዝ ባለፈ ለተቃውሞ የወጡትን ኢትዮጵያውያን በግፍ የማሰሩን ምክንያት ስንመረምር አንድ መራራ እውነት እንረዳለን፤ ይኸውም ጣሊያን ለኢህአዴግ መንግስት ዋንኛዋ ለጋሽ ሀገር መሆኗ ነው፡፡ ይህ የኢህአዴግ መንግስት ተግባር በስልጣን ዘመኑ በኢትዮጵያዊነት ላይ ከፈፀማቸው ክህደቶች እኩል በታሪክ ጥቁር መዝገብ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡ http://መረጃው የተገኘበት ማጣቀሻ/

Tuesday, March 26, 2013

ዳያስፖራው ኢትዮጵያዊ ሊመሰገን ይገባዋል!


ድምጻችን ይሰማ ተቃውሞ ያልተደረገበት የአሜሪካና የአውሮፓ ከተማ የለም ቢባል አልተጋነነም
ከዳያስፖራ ወገኖቻችን ገና ብዙ እንጠብቃለን

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሃይማኖታችን ገፍቶ የመጣብንን አደጋ ለመመከት ድምጻችንን አስተባብረን ተቃውሟችንን
ማሰማት ከጀመርንበት ቀን አንስቶ ከበርካታ ወገኖች በአይነትና በመጠን የተለያየ ድጋፍ ስናገኝ ቆይተናል፡፡ በዚህ
አይነቱ የትግል ወቅት ‹‹ድጋፍ›› ሶስት ፊደል ቃል ብቻ አይደለም - ወንድማዊ ትስስርን፣ በችግር ጊዜ የማይበጠስ
ጠንካራ ሰንሰለትን መፍጠር የሚችል ታላቅ ስጦታ ነው! ዛሬ ድጋፋቸውን ሲያበረክቱልን ከቆዩት ኢትዮጵያውያን
ወንድሞቻችን መካከል አንዱን ክፍል በምስጋናችን ልናወሳ ወደድን - ዳያስፖራውን!

ዳያስፖራው ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ለትግላችን ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ሁለንተናዊ ድጋፍ ለማበርከት
የቻለውን ሁሉ አድርጓል፡፡ እስካሁን ዳያስፖራው የእኛን ‹‹ድምጻችን ይሰማ›› ተቃውሞ ያላስተጋባበት የአሜሪካና
የአውሮፓ ከተማ የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ የዳያስፖራ ወንድሞቻችን ሰልፍ በርካታ ከተማዎችን አዳርሷል፡፡
ከኒውዮርክ እስከ ካናዳዋ ኦታዋ ዞሯል፡፡ ከዋሽንግተኑ ነጭ ቤተ መንግስት እስከ ስዊዘርላንዱ የተባበሩት መንግስታት
መስሪያ ቤት ደጅ ጠንቷል፡፡ የእንግሊዝ እና ስዊድን ከተሞችን አዳርሶ፣ ጀርመንን አልፎ የብራስልሱን አውሮፓ ህብረት
ቢሮ አንኳኩቷል፡፡ ፓሲፊክ ውቅያኖስን ተሻግሮ የአውስትራሊያዋን ሲድኒ ደጃፍ ረግጧል፡፡ የሰሜን አፍሪካዋን ግብጽ
ዳስሶ በታችኛዋ ደቡብ አፍሪካ ድምጹ ተሰምቷል፡፡ እስያ አህጉር ገብቶ ሪያድን ጅዳን አዳርሷል፡፡ ጥቂቶቹን እንዲሁ
ጠቃቀስናቸው እንጂ የኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች የ‹‹ድምጻችን ይሰማ›› ድጋፍ ሰልፍ ያልረገጠበት ቦታ የለም!
To read more please open http://www.assimba.org/Articles/YeDiasporaw_Misgana.pdf

Monday, March 25, 2013

በማእከላዊ እስር ቤት የታሰሩ ሙስሊም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው

መጋቢት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ የሚገኙ ከተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ተይዘው የታሰሩ ሙስሊም የዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ፣ ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ቦታ ባለማወቃቸው በቀለብ እና በልብስ እጦት እየተቸገሩ ነው።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችና መምህራን ታስረው እንደሚገኙ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ፣ ብዙዎቹ ቶርች ( አሰቃቂ ድብደባ) ተፈጽሞባቸዋል። በአሁኑ ጊዜ የረባ ምግብ አጥተው በመሰቃየት ላይ የሚገኙት ተማሪዎች ልብሶቻቸው በላያቸው ላይ እያለቁባቸው ለእርዛት መዳረጋቸውም ታውቋል።

የተለያዩ ታማሪዎች በየጊዜው እየተያዙ መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን በማእከላዊ እስር ቤቶች ውስጥ ታስረው ከሚገኙት መካከል የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ተማሪ የሆኑት ኑርየ ካሲም እና ካሊድ ሙሀመድ፣ የጅማ ዩኒቨርስቲዎቹ ያሲን ፈይሞ፣ ሙሀመድ አሚን ከድር፣ እና ጁነዲን ሁሴን፣ የሚዛን ተፈሪው አብዱላኪም አህመድ፣ የወሎ ዩኒቨርስቲዎቹ ጣሂር ሙሀመድ ፣ ሙሀመድ አብዱራሂም እና ሰኢድ ሙሀዲን፣ የጎንደር ዩኒቨርስቲዎቹ ሰኢድ አብርሀም ፣ኦማር ሙሀመድ፣ እና ሊና ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲው አብዱላዚዝ ሰኢድ እንዲሁም የአዋሳ ዩኒቨርስቲዎቹ አብደላ ሙሀመድ ይገኙበታል።

የሙስሊም ጉዳይ አምደኛ የነበረው ሶሎሞን ከበደ፣ የከሚሴው ዳኢ ጀማል ከበደ፣ የሻሸመኔው ዳኢ አብዱረዛቅ ሼህ አህመድ፣ የከሚሴው ዳኢ ኢክርሀም አብዱ፣ የሀረርጌው ሁሴን ሮባ፣ የድሬዳዋው ሙሀመድ ሀሰን፣ የከምሴው ሁሴን አሊ እና አደም አህመድ አሊ በማእከላዊ እስር ቤት ታሰሩት ከፍተኛ ስቃይ ከደረሰባቸው መካከል ይገኙበታል።
አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር መንግስታቸው እርምጃ እንደሚወስድ ሰሞኑን በባህርዳር በመካሄድ ላይ ባለው የኢህአዴግ ጉባኤ ላይ ተናግረዋል።

29 Ethiopian Commando Soldiers Defect to Eritrea

A total of 29 Ethiopian commando forces, who were trained in Blaten Special Force Institute, have defected to neighboring Eritrea.

yy
The soldiers vowed they will liberate Ethiopia from what they say is an oppressive and ruthless dictatorship, according to their communiqué released on Saturday.
Ethiopia is no stranger to high profile military defections. In 2005, eight Ethiopian air force pilots, who were training in Israel, defected and claimed asylum at an Eritrean embassy in Israel.Similarly, In 2006, over 300 Ethiopian troops, including Brigadier General Kemal Gelchu, who along with his trusted colonels, defected to Eritrea.

Jawar Mohamed speaks in Seattle

Jawar Mohamed: Diaspora role effective when supporting, and not dictating, home-based struggle
Ethiomedia; March 25, 2013
http://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=bi7mEEd1Xps
Published on Mar 25, 2013
SEATTLE - Political analyst Jawar Mohamed addresses various issues related to civil rights violations in Ethiopia, including the violations of religious freedom of Ethiopian Muslims. (March 23, 2013; Ethiomedia.com)



በቆብ ላይ ሚዶ (ሁለት) ፤ ትምህርትና ተማሪ ቤት



የዛሬዎቹ ባለሥልጣኖች በደርግ ጊዜ አልነበሩም፤ የደርግን ስሕተት በማየት አልተማሩም፤ ትምህርታን አቋርጠው ወደጫካ የገቡት ከትምህርት የሚበልጥባቸው ምኞት አጋጥሟቸው ነው፤ የትምህርት ገዜያቸውን በጫካ ባለሥልጣን በመሆን፣ እነሱው ሕግ አውጪና ዳኛ፣ እነሱው የጫካ አስፈጻሚ ሆነው ቀዩ፤ ደርግ በጠራራ ጸሐይ የሚሠራውን እነሱ በጫካ ጭለማ ሲሠሩ ቆዩ፤ በሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላም በጣም ቆይተው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን በትንሹ ተገነዘቡ፤ በጣም የተማሩ ሰዎች ጋር ሲገናኙ ማፈር አስጨነቃቸው፤ ስለዚህም ቀላሉ ነገር የተማሩ ሰዎችን አለማቅረብ፣ ትምህርታቸውን በጠባያቸው ካላጠቡ የተማሩ ሰዎች ጋር በቀር አለመገናኘት፣ እንዲያውም የትምህርትን ዋጋና ጥራት በማዋረድ አዲስ የሚመረቁት ሁሉ ለባለሥልጣኖች አንገታቸውን የሚደፉ ዓይነት እንዲሆኑ ማድረግ ዓላማ ሆነ።

የተማሩና የሠለጠኑ የጦር መኮንኖችም ተሸናፊዎች በመሆናቸው ትምህርታቸው ዋጋ እንደሌለው ማረጋጋጫ እያደረጉ የወያኔ መሪዎች በአደባባይ ተናገሩ፤ ትንሽዋ ቢምቢ ሰውን መግደል እንደምትችል ያልተገነዘቡት ከጫካ የመጡ ሰዎች በመግደል ማሸነፍን የትምህርትን ዋጋ-ቢስነት ማረጋጋጫ አደረጉት፤ የተማሩ ሰላማዊም የጦር መኮንኖችም ዋጋ-ቢስነታቸው ኑሮአቸውን በማናጋቱ በችግር ወደሌላ ሥራ ተሰማሩ፤ ወይም አገር ጥለው ተሰደዱ፤ በሰላማዊውም ሆነ በፖሊስና በጦር ሠራዊቱ የተማረ ሰው እጥረት መፈጠሩ ለወያኔ መግቢያና መደላደያ ምቹ ሁኔታን ፈጠረ።

በየትኛውም የሥልጣን ወንበር ላይ ለመቀመጥ ማናቸውም ዓይነት የትምህርት መመዘኛ ተሽሮ ሚዛኑ ስለተሰበረ ማንንም ከሜዳ እያነሡ በተፈለገው ወንበር ላይ ማስቀመጥ እየተለመደ ሄደ፤ በየሚኒስቴሩ ከመከላከያ ጀምሮ እስከአገር አስተዳደርና የውጭ ጉዳይ ወንበሮች ላይ የተደለደሉት ሁሉ ችሎታም ሆነ ብቃት ሳይኖራቸው ነበር፤ አንዳንዶች ብልጥ የሆኑት ከዱሮው መንግሥት ባለሥልጣኖች ውስጥ አንገታቸውን ደፍተው ሊሠሩ የሚችሉትን በጓዳቸው አስቀምጠው እንዲሠሩላቸው ያደርጉ ነበር፤ ቀንደኛ የኢሠፓ አባሎች ሳይቀሩ በጓዳ በር ተቀጥረው ነበር፤ በመሠረቱ የተማረ ሰው ለአሽከርነት አይመችም፤ ሆኖም የአሽከርነት ባሕርይ ያለው ሰው ቢማርም ትምህርቱ የባሕርዩን ጉድፍ አያጥበውም፤ አንዳንዶቻችን እንደምናውቀው ለአጼ ኃይለ ሥላሴም፣ ለኮሎኔል መንግሥቱም፣ ለመለስም በተከታታይ ታማኝ እየሆኑ ያገለገሉ ሰዎች አሉ፤ የማይታመኑ መሆናቸውን ያስመሰከሩ ሰዎች የሚታመኑበት አገር ከኢትዮጵያ ሌላ መኖሩን አላውቅም፤ ከኢጣልያ ወረራ ጀምሮ ይህ የእንጀራ ሎሌነት እየተለመደ ብሔራዊ ባሕርይ ወደመሆን እየተጠጋ ነው።

በትምህርትና በተግባር መሀከል ድልድይ የማይገኝለት ገደል ተፈጠረ፤ ትምህርት በሎሌነት! ሎሌ ለመሆን መማር! መማር ሎሌ ለመሆን! ሎሌነት ለአንድ ሰው፣ ሎሌነት ለአንድ ቡድን፣ ሎሌነት ለአንድ እምነት፣ ሎሌነት ለሆድ! አስቡት እንዲህ ያለ ሰው ምን ይማራል? ማን ያስተምረዋል? እንዴትስ ይማራል? ተምሮስ ምን ይሠራል? የተወረሰውን አንጎል ማጣጠብ ይቻል ይሆናል፤ አእምሮን ለሚያንጽ ትምህርት ግን ነጻነት ያለው አስተማሪ፣ ነጻነት ያለው ተማሪ፣ ነጻነት ያለበት መድረክ ያስፈልጋሉ፡፡

የሆነላቸው ባለሥልጣኖች ወደውጭ እየሄዱ ልዩ የአቋራጭ ሥልጠና እየተሳተፉ፣ አለዚያ አስተማሪዎች ለጥቂት ጊዜ እዚሁ መጥተው የአቋራጩን ሥልጠና በአጭር ጊዜ ውስጥ እየሰጡ፤ ‹‹ተማርን›› ብለው ራሳቸውንና ተከታዮቻቸውን አሳመኑ፤ ለምን የውጭ አገር ሰዎች አስፈለጉ? እነሱን ለማስተማር የሚችሉ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች አልነበሩም ወይ? እነዚህንና ሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄዎች አእምሮአቸው ማንሣት ባይችልም ወዳጅ ዘመዶች ሳይነግሯቸው የቀሩ አይመስልም፤ ግን እንዲህ ያለውን ምክር መቀበል አላዋቂነታቸውን ማጋለጥ ስለሚሆን ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም!

የትምህርት ጊዜያቸውን ሥልጣንን በማሳደድ ለውጠው ሳይማሩ የቀሩት ከፍተኛ የአገር ገንዘብ ወጪ እያደረጉ በስማቸው ላይ የሚጨምሩት ምልክት የትምህርትን እውነተኛ ፍቺ እንዳልተገነዘቡ የሚያሳይ ነው፤ የትምህርት ማዕርጎች ከቢ.ኤ. ጀምሮ እስከፒኤች.ዲ. የትምህርት ቤት በራፉን ሳይረግጡ በግዢ ሊገኙ ይችላሉ፤ በግዢ የሚገኘው የምስክር ወረቀት እንጂ ትምህርት አይደለም፤ ለመሆኑ ኢትዮጵያን ያህል አገር እያስተዳደሩ የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ለመከታተል ይቻላል ወይ? ከተቻለ ወይ አገር መግዛቱ ጨዋታ ነው፤ ወይ ትምህርት የተባለው ጨዋታ ነው፤ ወይም ሁለቱም ጨዋታ ነው፤ ያለትምህርት አገር መግዛት ጨዋታ ነው፤ ያለሥርዓት ትምህርት ጨዋታ ነው፤ ለአዋቂ ሰው በጥንት ነገሥታት ዘመንም ቢሆን ያው ነበረ የሚል ክርክር ማንሣቱ ራስን ያጋልጣልና የሚበጅ አይመስለኝም፤ በቆብ ላይ ሚዶ ጌጥ አይሆንም፤ ጥቅምም የለው፤ ከቆቡ ስር ያለው መላጣ ቢሆንስ!
በትዕቢት የተወጠሩት በአገር ላይ ባለሙሉ ሥልጣን የሆኑት ሰዎች የትምህርትን መሠረታዊ ባሕርይ ስተውታል፤ በመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት በተወሰነ የእድሜ ክልል ውስጥ ወደተማሪ ቤት ለብዙ ዓመታት እየተመላለሱ የሚያገኙት እውቀት እንጂ በሥልጣን ወንበር ላይ ተቀምጠው እያዘዙ እንደዕቃ የሚያስመጡት አይደለም፤ መማር ደረጃ በደረጃ አስተማሪዎች የሚሰጡትን ትምህርት ተከታትሎ ፈተናዎችን እያለፉ የሚጓዙበት የእውቀት ጎዳና ነው፤ ትምህርት የአስተማሪና የተማሪ ግንኙነት ነው፤ አስተማሪና ተማሪ ማለት አዋቂና አላዋቂ ማለት ነው፤ በየኔታ(የኔ ጌታ)ና በልጅ መሀከል ነው፤ አስተማሪው የተማሪውን አእምሮ በሕገ ኀልዮት፣ ጠባዩን በሥነ ሥርዓት እየገራ፣ እየተቆጣ፣ እየኮተኮተ የሚያሳድግ ነው።

ትምህርት በተማሪዎች መሀከል ያለ ግንኙነት ነው፤ ተማሪዎችን የሚገራው አስተማሪው ብቻ አይደለም፤ ተማሪዎቹም እርስበርሳቸው አንዱ ከሌላው የሚማረውና የሚገራበት መንገድ ብዙ ነው፤ እርስበርሳቸው እየተቀላለዱ፣ እየተሰዳደቡ፣ እየተራረሙ፣ እየተፎካከሩና እየተገማመቱ የሚያድጉበት ሥርዓት ነው፤ ስለዚህም ተማሪዎች ትምህርት የሚያገኙት ከአስተማሪዎች ብቻ አይደለም፤ ይህ ሁሉ ሁኔታ በሌለበት በሥልጣን ወንበር ላይ ተኮፍሶ በሎሌነት በግል የተቀጠረውን አስተማሪ ወደታች እያዩ መማር የሚቻለው እንዴት ነው? መማር ማለት ወደላይ እያዩ ነው፤ ወደታች እያዩ መማር አይቻልም፤ አንድ ሰው ስለህክምና ምንም ሳይማር አውቃለሁ ብሎ ሥራ ከጀመረና አጉል መድኃኒት እየሰጠ የባሰ ሲያሳምምና አካልን እየቀደደ መልሶ መስፋት ሲያቅተው፣ በኋላ ሕመምተኞቹን አጋድሞ ህክምና ልማር ብሎ አስተማሪ ቢፈልግ ምን ይባላል?

ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ ተርፈው ብዙ ሌሎች አገሮችን አዳርሰዋል፤ የወያኔ ሹሞች ግን በከፍተኛ ወጪ ከአሜሪካና ከእንግልጣር የውጭ አገር ሰዎችን ሲያስመጡ የነበረው አንደኛ በኢትዮጵያዊ ተበልጠው ላለመታየት፣ሁለተኛ የአለማወቃቸውን መጠን እንዳይናገር ሹልክ ብሎ ገብቶ ሹልክ ብሎ ሳይታወቅ ቶሎ ወዳገሩ የሚመለስ የውጭ ሰው በማስፈለጉ፣ ሦስተኛ የገንዘብ ችግር ስለሌለ ነው።

ባለሥልጣን ሆኖ አላዋቂ መሆን ያሳፍራል፤ አዋቂ መስሎ አላዋቂ ሆኖ መገኘት የባሰ ያሳፍራል፤ ሳይማሩ በጉልበት ባለሥልጣን መሆን ሰውዬውን ራሱን የሚያሳፍርበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፤ ያፈረ ባለሥልጣን በጎ ነገርን አያስብም፤ በየሳምንቱ አንዳንድ ለጆሮ የሚቀፉና አገርንና ሕዝብን የሚጎዱ ነገሮችን እንሰማለን፤ አይታረሙም፤ የሚናገሩት ክፉ ነገር ነገ ክፉ ውጤትን ሊያስከትል እንደሚችል አያውቁም፤ ሥልጣን አፋቸው እንዳመጣ እንዲናገሩ ያስችላቸዋል፤ አለመማራቸው ከዚያች ቅጽበት አልፈው እንዳያዩ ይጋርዳቸዋል።
እድገት የሚመጣው ትምህርት በነጻነት ሲመራና፣ ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ሲያዝ ነው፤ ሥልጣን በነጻነት፣ ትምህርት በቁጥጥር የቁልቁለት መንገድ ነው።
መስፍን ወልደማርያም
ጥር 2005

Saturday, March 23, 2013

እንጩህ፡፡ መንግስት ሰምቶ አቤት እንዲለን ሳይሆን ህዝብ ሰምቶ እንደኛ እንዲጮህ እንጩህ!!

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ሂደት ውስጥ መንግስት በተቃዋሚ ኃይሎችና በጋዜጠኞች ላይ በተከታታይ የወሰዳቸው አሸማቃቂ እርምጃዎች የተለያዩ ውጤቶች አስከትለዋል፡፡ ከነዚህ ውጤቶች መካከል ዝምታ በጣም አስከፊው ነው፡፡ ዝምታውን በሁለት መክፈል ይቻላል፡፡
አንደኛው የብዙሃኑ ዝምታ ነው፡፡ የዚህ ዝምታ ምንጭ በአመዛኙ ከፍርሃት የመነጨ ይመስለኛል፡፡ በስርዓቱ ላይ ያለውን ተቃውሞ ለመግለፅ የፍርሃቱን ምህረት የለሽ ቅጣት በመፍራት በአገሪቱ ላይ የሚፈፀሙ ግፎችን በዝምታ ይመለከታል፡፡
ሁለተኛው ዝምታ የተቃዋሚው፣ የምሁራንና የጋዜጠኞች ዝምታ ነው፡፡ የዚህ ዝምታ ምክንያት ደግሞ ተስፋ መቁረጥ ይመስለኛል፡፡ የስርዓቱን እርምጃዎች በመተቸትና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እይታቸውን በማካፈል የሚታወቁት አብዛኞቹ ሰዎች በስርዓቱ ላይ ተስፋ በመቁረጣቸው የመንግስትን እርምጃዎች መተቸትን ተራራ እንደማጠብ ቆጥረውታል፡፡ በዚህ መካከል ግን የልማታዊ መንግስት ስርዓት እየወፈረና እየፋፋ መሄዱን ቀጥሏል፡፡

በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሃሳብን መግለፅና በድንቁርና መሰረት ላይ የቆመውን የልማታዊ መንግስት ስርዓት መፈተን እየተቻለ ዝምታን አማራጭ ማድረግ ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ ጉዳቶች ያስከትላል፡፡

አንደኛው፣ ዜጎች በመንግስት እርምጃዎች ሁሉ እየተስማሙ ወይም ሳይከነክናቸው እንዲቀጥሉ ያደርጋል፡፡ ይህም የሚሆነው በአማራጭ ሃሳቦች እጦት ነው፡፡ ትንሽ አማራጭ ሃሳቦች ማግኘት ያልቻለ ህዝብ የመንግስትን ሃሳብ እየተቸገረም ቢሆን ይውጣል አለበለዚያም ከአገራዊ ጉዳዮች ራሱን አግልሎ በሌሎች እንቶ ፈንቶ ወሬዎች ይጠመዳል፡፡ ይህ ደግሞ ልማታዊ ስርዓቱን በማይናወጥ መሰረት ላይ ያቆመዋል፡፡ ለወደፊቱም ለዲሞክራሲ የማይመች ማህበረሰብ እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡
ሁለተኛው የዝምታው ጉዳት መንግስት ከአሁን በፊት እየተግደረደረም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚቀበላቸው የተቃውሞ ሃሳቦች ምንጫቸው እንዲደርቅ ማድረጉ ነው፡፡ በዚህም የመንግስትን እርምጃዎች ሙሉ በሙሉ የ’እንደልቡ’ እርምጃዎች ያደርጋቸዋል፡፡ ተቃውሞን ፈርቶ የሚያለሳልሰው እርምጃ ወይም አቋም ሊኖር አይችልም፡፡ ይህም የስርዓቱን ጉልበት በመጨመር መከራችንን ያበዛዋል፡፡

ስለዚህም ከዝምታ ዋሻችን ወጥተን የሚሰማንን በመግለፅ ኮርማውን ከውፍረት እንታደገው፡፡ ፌስቡክንና ትዊተርን የመሳሰሉ የማህበረሰብ ድሮችን ጨምሮ ሌሎች የተገኙ መንገዶችን በመጠቀም ሃሳባችንን እንግለፅ፡፡ ልማታዊ መንግስቱን መታገል የሚቻለው የሃሳብ ሚሳኤል በማስወንጨፍ ነው፡፡ ከሃሳብ በላይ የሚያፈርሰው ኃይል ሊኖረው አይችልም፡፡ ጠብመንጃን ከመከላከል በላይ ሃሳብ እንዳይገለፅ ለመከላከል ተግቶ የሚሰራውም ለዚህ ነው፡፡ ዝምታችን የስርዓቱ ዋስትና ነው፡፡
መልዕክቴ ይህ ነው- እንጩህ፡፡ መንግስት ሰምቶ አቤት እንዲለን ሳይሆን ህዝብ ሰምቶ እንደኛ እንዲጮህ እንጩህ፡፡ ስርዓቱን በጩኸት እናፍርሰው፡፡ 
http://walelgnemekonnen.wordpress.com/2013/03/22/lets-mobilize-the-people-by-shouting/

እንደ አምላክነቱ መከበር ሳያንሰው ሊያገለግል መጣ የጌታ ልጅ ለሰው።

http://www.facebook.com/photo.php?v=330235477010626&set=vb.100000725295083&type=2&theater

የጽድቅን ጎዳና ላለም ኣስተምሮ
ሔደ ወደ ኣባቱ መቃብሩን ሰብሮ

Alle, unntatt Frp, mener at innvandrere er ressurs for Norge



Bred enighet om hovedlinjene i norsk integreringspolitikk da Stortinget i dag diskuterte Regjeringens stortingsmelding. Bare Fremskrittspartiet skiller seg ut som den store kritikeren.


 arne-, likestillings- og inkluderingsminister Inga Marte Thorkildsen
FOTO: Junge, Heiko 

Fremskrittspartiets medlemmer er de eneste i Stortingets kommunal- og forvaltningskomité som ikke deler Regjeringens syn på innvandring som ressurs for Norge. De vil dermed heller ikke være med på å fremheve den betydning som 300.000 sysselsatte innvandrere har for verdiskapningen og velferdsproduksjonen i Norge.

De andre partiene, inkludert Venstre, er enige om hovedtrekkene i norsk integreringspolitikk. Det ble klart da Stortinget i dag behandlet stortingsmeldingen «En helhetlig integreringspolitikk. Mangfold og fellesskap». Likevel er det enighet på Stortinget om at det er noen utfordringer.

Inkluderingsminister Inga Marte Thorkildsen sa at meldingen legger stor vekt på å øke sysselsettingen og norskferdighetene blant innvandrere.

- Likevel har innvandrerkvinner i Norge høyere sysselsetting enn kvinner generelt i Italia, sa hun. les mer fra linken http://www.aftenposten.no/nyheter/iriks/Alle_-unntatt-Frp_-mener-at-innvandrere-er-ressurs-for-Norge-7154532.html#.UU3NnXYkmdk

Friday, March 22, 2013

ከጠቅላይ ፍ/ቤት እስከ ሚንስትሮች ም/ቤት

ተመስገን ደሳለኝ

መጋቢት 18/2005 ዓ.ም የእነ እስክንድር ነጋ ይግባኝ ለመጨረሻ ጊዜ ተብሎ ተቀጥሯል፡፡ በዚህ መዝገብ የተከሰሱት የህሊና እስረኞች ይግባኝ ከጠየቁ አምስት ወር አልፏቸዋል፡፡
ለምን? …በአዲስ መስመር እንነጋገርበት፡፡
የይግባኙን ውሳኔ ያዘገየው የፖለቲካ ተንታኝ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የተከሰሰው በሀሰት ስለሆነ ነው፡፡ በእርግጥ ይህንን ያልኩት እኔ አይደለሁም፤ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የመሀል ዳኛ የሆነው አቶ አማረ አሞኘ ነው፡፡ ባለፈው ወር ዳኛው አቃቢ ህጎቹን ሰበሰበና እንዲህ አላቸውከጠቅላይ ፍ/ቤት እስከ ሚንስትሮች ም/ቤት
፡-‹‹ይህን ሰው አሻባሪ ነው ብላችሁ ስትከሱት ያቀረባችሁት ማሰረጃ በተለያየ ጊዜ የፃፈውን ፅሆፎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና በአንድ የፖለቲካ ፓርቲ መድርክ ላይ ተናገረው ያላችሁትን ብቻ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ፅሁፉና ንግግሩ ያስከተለው አደጋ አልተገለፀም፤ ወይም ምንም አይነት አደጋ አላስከተለም ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተከሳሹ ላይ ቅጣት ለመጣል አያስችልም፡፡ ስለዚህም ሌላ ጥፋተኝነቱን የሚያረጋግጥ ማሰራጃ ካላችሁ አቅርቡ? አሊያም በሚቀጥለው ቀጠሮ ሲቀርብ በነፃ እለቀዋለሁ፡፡›

.አቃቢ ህጎቹ ምንም ማስረጃ አልነበራቸውምና በደፈናው ‹‹ሰውየው አሸባሪ ስለሆነ ዝም ብለህ፤ ይግባኙን ውድቅ አድርግና የከፍተኛው ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አፅናበት›› የሚል ይዘት ያለው ተመሳሳይ አቋም አንፀባረቁ፡፡ ዳኛው ምን አይነት መንፈሳዊ ኃይል ተጭኖበት እንደ ሆነ እንጃ! ‹‹በፍፁም ከህግ ውጪ አልሰራም፤ ህሊና አለኝ›› ብሎ ፍንክች ያባ ቢለዋ ልጅ ይላል፡፡
ይህን ጊዜም ነገሩ ቦግ ያደረገው አንድ አቃቢ ህግ
‹‹አንተ እስክንድርን እለቃለሁ የምትለው ያገርህ ልጅ ጎንደሬ ስለሆነ ነው!››
ይለዋል ቁጣ በተቀላቀለበት ድምፅ፡፡ ዳኛ አማረም ይበልጥ ተናዶ
‹‹እኔ እሰከ ዛሬ ድረስ ያገለገልኩት ሀገሬን ኢትዮጵያ እንጂ የትውልድ መንደሬን አይደለለም፡፡ ደግሞም ዘረኝነት የለብኝም›› ሲል መለሰለት፡፡
በእንዲህ አይነት ሁኔቴ መዋዘገቡ በመካረሩ መግባባት አልቻሉምና ጉዳዩ ሚንስትሮች ምክር ቤት ደረሰ፡፡ በሚንስትሮች ም/ቤትም ስብሰባውን የመራው ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ደመቀ መኮንን ሲሆን፣ ዳኛውም አብሮ ቀርቧል፡፡ አቶ ደመቀ መጀመሪያ ዳኛው ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠየቀ፡፡ ዳኛውም ስለክሱ አጠር አድርጎ ካብራራ በኋላ እንዲህ ሲል ደመደመ፡-
‹‹እስክንድር ነጋን ‹አሸባሪ› ብሎ ለመፍረድ የሚያስችል በቂ ማስረጃ ስላልቀረበ በሚቀጥለው ቀጠሮ በነፃ አሰናብተዋለሁ፤ እንዲህ ማድረግ አትችልም የምትሉኝ ከሆነ ግን ክቡራን ሚንስትሮች በዕለቱ በችሎት ለመሰየም ፍቃደኛ አለመሆኔን በትህትና ትረዱኛላችሁ ብዬ አስባለሁ!››
ከዚህ በኋላ ሚኒስትሮቹ መወያየት ጀመሩ፡፡ ተከራከሩ፤ በመጨረሻም አቶ ደመቀ እንዲህ አለ፡-
‹‹እኔም ከአቶ አማረ ጋር እስማማለሁ፡፡ ምክንያቱም በዚህ ሰውዬ /እስክንድር/ የተነሳ ከፍተኛ አለም አቀፍ ጫና እየደረሰብን ነው፡፡ ስለዚህም ብንፈታው ተጠቃሚዎቹ እኛው ነን ብዬ አስባለሁ፡፡››
አንድ ሚኒስትር ቀጠለ፡-
‹‹በመሰረተ ሃሳቡ ላይ እስማማለሁ፡፡ ነገር ግን እስከዛሬ አስረነው ‹ነፃ ነህ› ብለን ብንለቀው የፖለቲካ ኪሳራ ስልሚያስከትልብን፣ ከፍርዱ ላይ ቅንስናሽ አድርገን ይቅርታ ጠይቆ እንዲወጣ ብናደርግ የተሻለ ነው፡፡››
ሌላ ሚኒስትር ቀጠለ፡-
‹‹እስክንድርን እኔ አውቀዋለሁ፤ የአሜሪካን ሀገር መኖሪያ ፍቃድ እና ብዙ ሀብት እያለው እዚህ ነገር ውስጥ የገባ ሰው ነው፡፡ እናም በፍፁም ይቅርታ ለመጠየቅ ፍቃደኛ አይሆንም››
ሌላኛው ሚንስትር ቀጠለ፡-
‹‹ኧረ ለመሆኑ መለስ አለም አቀፍ ጫና እንደሚያስከትል እያወቀ ለፓርቲያችን ጥቅም ብሎ የገባበትን ጉዳይ፣ ዛሬ እርሱ አልፏል ብለን ጫና ይምንፈራበት ምክንያት ከየት የመጣ ነው? በቃ! መለስ አደገኛ ሰው ነው ብሎ አስሮቷል፡፡ አለቃ! እዛው ይበስብስ!››
የሚንስትሮች ምክር ቤትም ቢዚህ ጉዳይ ላይ መስማማት ሳይችል በመቅረቱ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዘዳንት አቶ ተገኔ ቀርቦ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ቀጠሮ ይዘው ተለያዩ፡፡
…በእርግጥ ከአቶ ተገኔ ማብራሪያ በኋላ የሚኒስትሮች ም/ቤት ምን አይነት አቋም ላይ እንደደረሰ ለማወቅ ያደረኩት ጥረት ሊሳካ አልቻለም፡፡ መረጃውንም እስከ ዛሬ ያቆየሁት ለዚህ ነበር፡፡ አሁን ግን የቀጠሮ ቀን ሰለደረሰ ልነግራችሁ ተገደድኩ፡፡
እናም የፊታችን ረዕቡ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሚከተሉት አራት ነገሮች አንዱን እናያለን ብዬ አስባለሁ፡፡
1. የሚንስትሮች ም/ቤት ጫናው ስለከበደው በነፃ ይለቀዋል፣
2. መለስ እያወቀ የገባበትን ጫና አንፈራም! (ራዕዩ እናስቀጥላለን እንደማለት ነው) በማለት የከፍተኛውን ፍርድ ቤት ውሳኔ ያፀናሉ፣
3. ከተፈረደበት 18 ዓመት ላይ ቅንስናሽ አድርገው፣ ይቅርታ እንዲጠይቅ ወደ ማግባባቱ ይሄዳሉ፣
4. ዳኛው አሞኘ እንደፎከረው ከችሎቱ ይቀርና አሁንም
‹‹የመጨረሻ›› ቀጠሮ ይሰጣል፡፡
የሆነ ሆኖ እንዲህ የሚል አንድ እውነት ‹‹በመሪዎቻችን›› ግንባር ላይ ተቸክችኳል፡፡ ‹‹ሲቪሉ ጀግና እስክንድር ነጋ እያርበደበደው ነው!››
አዎ! እኔም እላለሁ፣ የእስክንድር እና መሰሎቹ የግፍ እስር አርብድብዶ ብቻ አይተዋችሁም!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ! ውድቀት ለአምባገነኖች!!

Thursday, March 21, 2013

የትግራይ ህዝብ ስማ!!


mekelle

(ርዕሰ አንቀጽ) March 21, 2013
ሰሞኑን በውዴታም ይሁን በግዴታ በመቀሌ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ሲጨፍሩ፣ ሲዘሉ፣ ከበሮ እየመቱ የባህላቸውን ዘፈንና ውዝዋዜ ሲያወርዱ አይተናል። ምክንያቱ በግልጽ ባይነገርም ሲደበቅ የነበረው የህወሃት ሃብትና ንብረት ውጤት የሆኑ፣ በልዩ የመንግስት ድጋፍ የተከናወኑ ግዙፍ ተቋሞች በጎዳና ለህዝብ ሲቀርቡም ተስተውሏል። ልማቱ መልካም ነው። ደስ ይለናል። ምንም ተቃውሞ የለንም። ግን መልዕክት አለን።

ለማን?
ምሬትን፣ ጭቆናና መንገፍገፍ ሲበዛ በፍቃደኛነት በቦንብ ላይ እንደሚያስሮጥ ለሚያውቀው የትግራይ ህዝብ!! የትግራይ ህዝብ ስማ!!
ሰሞኑን ይፋ የሆነው የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ሪፖርት የትግራይ ክልል በትምህርት፣ በኤሌክትሪክ፣ በመንገድ፣ በእርሻ፣ በደን፣ በኢንዱስትሪ፣ በጤና፣ ወዘተ ከሌሎች ክልሎች ሁሉ ርቃ መሄዷን ይፋ አድርጓል። በዚህም ደስ ይለናል። አይከፋንም። ከዚህ በላይ እንዲሆን እንመኛለን። ነገር ግን አንድ መልዕክት አለን።

ለማን?
አሁንም ለትግራይ ህዝብ!!
ሓውዜን የትግራይ ወጣቶች ለትግል ግልብጥ ብለው እንዲወጡ አደረገ። ሓውዜን የደረሰው የቦንብ ድብደባ ማንና እንዴት እንደተቀነባበር ብዙ የሚባልለት ቢሆንም የምሬት ጫፍ ሆኖ ህዝብን አሸፍቷል። ዛሬ መጨቆን ያንገፈግፋል ብለው ለትግል በተነሱና በተሰው ታጋዮች ደምና አጥንት ላይ የቆሙ ሌሎች ሓውዜኖች እንዲፈጠሩ አድርገዋል። እያደረጉም ነው።

ይህ በማን ስም እየሆነ ነው? በህወሃት አማካይነት በትግራይ ህዝብ ስም!!
ኦሮሚያ ልጆቿን በእስርና በጥይት እያጣች ነው። በጨለማ ቤት እየተሰቃዩ ያሉ የኦሮሞ ልጆች ግፍ ሰፍሮ ሞልቷል። አማራው አገር አልባ ሆኖ በየጎዳናው እየወደቀ ነው። እየተለዩ ከየክልሉ እየተባረሩ ነው። የመኖር ዋስትናቸውን ተከልክለው በሞትና በጣር መካከል ያሉ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ለቅሶ ሰማይ ደርሷል። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሎ እስር ቤት የሚማቅቁና የሚሰቃዩ ሰውነታቸውም የሚተለተል አሉ። የተገደሉ አሉ። ይህንን የሚያደርገው ደህንነቱ የተቆጣጠረውና መሳሪያ ያነገተው ኃይል ነው። ይህ ኃይል ደግሞ ህወሃት ነው። ህወሃት ይህንን ሁሉ ግፍ የሚፈጽመው በትግራይ ህዝብ ስም ነው። እያመረተ ያለው ደግሞ ብዙ ሓውዜኖችን ነው። በደልና የበቀል ስሜት ላንድ ጎሳ ወይም ሕዝብ ብቻ የተሰጠ አይደለምና ሌሎችም ሊነሱ ይችላሉ። መቼና እንዴት? አይታወቅም። በሲዳማ፣ በሶማሌ፣ በአፋር፣ … ብዙ ችግርና ምሬት አለ።

በጋምቤላ ግፍ ነዶውን እየወዘወዘ ነው። በጋምቤላ በዘመናት ወደፊት የማናገኛው የደን ሃብት እየወደመ ነው። በጋምቤላ ሰላማዊ ህዝቦች ከቀያቸው እየተፈናቀሉ መሬታቸውን እየተነጠቁ ለውጪ “ባለሃብቶች” እንዲሁም ለትግራይ ተወላጆች እየተከፋፈለ ነው። በባሌ፣ በቦንጋ፣ በወለጋ፣ ድፍን ኦሮሚያና የደቡብ ክልል ደን እየተጨፈጨፈ ትግራይ በደን እየተሸፈነች ነው ብሎ መጨፈር ለትግራይ ህዝብ ኩራት አይሆነውም። ኢትዮጵያዊ ነው የሚባለው የትግራይ ህዝብ እሱ የሚጠላውና ልጆቹን የገበረለት ግፍ በሌሎች ወገኖቹ ላይ ሲፈጸም ዝም ማለቱ ለምንና ከምን የመነጨ እንደሆነ ለማወቅ የሚፈልጉ አሉና ጥያቄውን እናቀርባለን።

ስለመፈናቀል ስናወራ “የትግራይ ተወላጆች ተፈናቀሉ” ሲባልና “ተፈናቀልን” ብለው ቅሬታና አቤቱታ ሲያቀርቡ አንሰማም። ይልቁኑም የአማራን ለም መሬት ለትግራይ በመከለል በደል የሚፈጽመው ህወሃት የሚባለው በትግራይ ህዝብ ስም የተደራጀና በነጻ አውጪ ስም እስካሁን አገር የሚመራ ቡድን ነው። ይህ ሁሉ ሲደረግ የትግራይ ህዝብ ያውቃል። ቢያንስ ቢያንስ የሰው መሬት ወርረው የተቀመጡት አይክዱትም። ግን ይህ እስከመቼ ይቀጥላል? ፍርሃት አለን። ለምን? ይህ ሁሉ ሌላኛው የሓውዜን ክፍል ነዋ!!

ስለ ግብር ሲነሳ የትግራይ ተወላጆች በግብር ዕዳ፣ በባንክ እዳና እንደ ልብ ነጻ ሆኖ በመንቀሳቀስ ችግር ቅሬታ ሲያሰሙ አይደመጥም። በመላው አገሪቱ በኢንቨስትመንት ተሰማርተው በሰላም እየሰሩ ነው። ሌሎች ግን በብሔር ተለይተው መከራ ይደረስባቸዋል። ህወሃት በማንነታቸውና ባመለካከታቸው እየነጠለ ከጨዋታና ከኑሮ መስመር ያወጣቸዋል። የጭቃ ቤት፣ አርሰው የሚበሉበት ከብት፣ ዶሮና በግ ሃብት ተብሎ ይወረስባቸዋል። ይህ እውነት ለትግራይ ምሁራን የተሰወረ አይደለም። ይህም ሌላው ህወሃት በትግራይ ህዝብ ስም በሌሎች ዜጎች ላይ የሚፈጥረው የምሬት ሓውዜን ነው!!

ኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ ሲነሳ የመጀመሪያው መስመር ላይ ሆነው አገሪቱን የሚያልቡት የቀድሞ ታጋዮችና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ነጋዴዎች ናቸው። ጤፍ ወደ ኤርትራ በማጋዝ፣ ባህር ዛፍና ቡና በማሻገር፣ የዱር እንስሳትን ቆዳና ቀንድ በመነገድ የተሰማሩት ይታወቃሉ። ብዙ እጅግ ብዙ ማለት ይቻላል። የምናነሳቸው ማሳያዎች ሁሉ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ፣ … ሓውዜኖች ናቸውና እዚህ ለጊዜው ላይ  እናቁም!!

ሻዕቢያ ድንገት ወረራ አካሂዶ ድፍን ትግራይን ሲቀጠቅጥ፣ ህጻናትን በቦንብ ሲቆላ፣ አገሬ ብሎ የተነሳን ህዝብ በማያውቀው ወንጀል እየሰፈሩ ማሰቃየት ይቆም ዘንድ የትግራይ ህዝብ በቀጥታ ድምጹንና ተቃውሞውን በአግባቡ ማሳየት የሚገባው ወቅት ላይ እንደሚገኝ ይሰማናል፤ ደግሞም እናምናለን። ዛሬ “ውርሱን እንጠብቃለን” በማለት የሚጮህላቸው አቶ መለስ በወቅቱ ክህደት ሲፈጽሙ የደረሰው ዛሬ እየተነጠሉ የሚመቱትና መድረሻ ያጡ ወገኖች ናቸው። ዛሬም ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ናቸው። በሰባና ሰማንያ ሚሊዮን ህዝብ ልብ ውስጥ የተፈጠሩት ሓውዜኖች ወደ ቁጣ ሲለወጡ አምስት አምስት ሆኖ መደራጀት፣ በስውር መታጠቅና በየሰፈሩ ያሉትን አስተባባሪዎች ስም ለቅሞ በመያዝ “ሳልቀደም ልቅደም” ብሎ መራወጥ አያዋጣም፤ ጊዜው ስለሚያልፍበት የትም አያደርስም። ሓውዜናዊ ህይወት የሚኖር ሕዝብ ከደረሰበት በላይ የሚያጣው ስለማይኖር እንኳን ስለማጣት ስለመኖርም አያስብም፡፡ በዚህ ከቀጠለ የቀን ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በየቦታው ራሱ ህወሃት የፈጠራቸው ሓውዜኖች መናደፍ መጀመራቸው አይቀርም።

“ህወሓትን እናስቀድም … ጠላቶቻችንን እናጥፋ” በሚል የማያቋርጥ ጥላቻ መቀጠል ተጨማሪ ሓውዜኖችን ከመፍጠር በስተቀር “ጠላትን” ማጥፋት የማይቻል እንደሆነ ከዚህ በፊት በሕዝብ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የወሰዱ ተሞክሮ ማስረጃ ነው፡፡ በበረሃ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ሥልጣን ይዞ “ጠላትን እናጥፋ”፤ አገር እየመሩ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮ “ጠላትን እናጥፋ” … 40ዓመት ሙሉ በ“ጠላትን እናጥፋ” መርህ የሚጓዘው ህወሃት “ጉድጓድ የሚምስ ራሱ ይወድቅበታል” የተባለው የተቀደሰ አባባል ሲፈጸም እንዳየነው ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ለማጥፋት የሚመኘው ህወሃት የራሱ መጥፊያ የሆኑ በርካታ ሓውዜኖችን ፈጥሯል፡፡

“የ100 ዓመት የቤት ስራ ሰጥተናቸዋል” በሚል በየድረገጹ የሚለጠፉ ተራ ድንፋታና ትዕቢት የሚፈጠሩትን ሓውዜኖች ከማብዛት ውጪ ትርፍ የላቸውምና ወደ ደጉ መንገድ መመለስና ሰብዓዊነትን በማስቀደም፤ ተደጋግፎ መኖርን ማጎልበት ይሻላል ለማለት እንወዳለን። ተሳስበውና ተረዳድተው የሚገነቡት የትም ሆነ የት የአገር ነውና ሁሉም ይኮራበታል፤ ይጠብቀዋል። ተጠቃሚ ይሆንበታል። የሚያምርብንም ይህ ነው። ህወሃት አልሰማም ብሏል። የትግራይ ህዝብ ግን ስማ!! ይህ ሁሉ የሚደረገው በስምህ ነው!! መረጃው የተወሰደው ክጎልጉል የኢንተርኔት ጋዜጣ ነው። ይጎብኑት ለተጨማሪ መርጃዎች

Wednesday, March 20, 2013

የፍትሕ ሁኔታ በትግራይ (ኣብርሃ ከመቐለ)

ኢ.ኤም.ኤፍ – ይህ በስፍራው ከሚገኘው ኣብርሃ ደስታ የተገኘ የትዝብት ዘገባ ነው። እንዲህ ብሎ ይጀምራል።

ኣንድ ኣቶ ግርማይ ጀርመን ትናንት ማታ በዋስ ተለቀዋል። በኣክሱም ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ያለ ምክንያት (ወይ ግልፅ ባልሆነ ምክንያት) ታስረው የሚሰቃዩ ንፁህ ዜጎች እንዳሉ ጠቁመዋል። እስረኞቹ የግል ሚድያዎች በኣክሱም ወህኒ ቤት ያለ መጨናነቅ እንዲዘግቡና እንዲያጣሩ ተማፅነዋል። በትግራይ የፍትሕ ስርዓቱ የተዛባ ከመሆኑ የተነሳ ወንጀል ፈፅመው የታሰሩ (ለምሳሌ ‘ዓዲ ሃገራይ’ ተብሎ በሚጠራ ኣከባቢ ሁለት ልጆች በግፍ የገደሉ ሰዎች) ጥሩ እንክብካቤ ሲደረግላቸው ምክንያቱ በማይታወቅ (ወይ በፖለቲካ) የታሰሩ ግን ብዙ ችግር እንደሚደርስባቸው ተገልፀዋል።

ሁለት በትግራይ ‘ፈረስ ማይ’ በሚባል ቦታ ዉሃ ከጠፋ ኣራት ወራት ቢያልፍም የሚመለከተው ኣካል መፍትሔ ሊሰጥ ባለመቻሉ ነዋሪዎቹ ለብዙ ዉሃ ወለድ በሽታዎች መዳረጋቸው ለማወቅ ተችለዋል። ኣስተዳዳሪዎች ለፖለቲካዊ ስብሰባዎች ብቻ እንጂ የህዝብ ማህበራዊ ችግሮች ግዜ እንደማይሰጡ ይነገራል።

ሦስት በደጉዓ ተምቤን ልዩ ስሙ (ቁሸት) ‘ድንግለት’ (ሀገረ ሰላም ኣከባቢ መሆኑ ነው) በሚባል ኣከባቢ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ወደ ቤተክርስትያን (እንዳ ማርያም) እየሄዱ ፖለቲካ ስለሚሰብኩና ዕዳ ያለባቸው ኣባወራዎች ስለሚያስሩ የኣከባቢው ሰዎች ወደ ቤተክርስትያኑ ላለመሄድ በመኃላ ኣድማ እንደመቱና የቤተ ክርስትያኑ ቄሳውስት ሁኔታው በመረዳት ካድሬዎቹ ከተግባራቸው እንዲቆጠቡ ቢመክሩም ሰሚ ስላላገኙ ወረዳ ሄደው መክሰሳቸው ታውቀዋል።

ኣራት በውቅሮ ኣከባቢ በሚገኝ ኣንድ ትምህርትቤት ተማሪዎች ለህወሓት ድጋፍ ሰልፍ እንዲወጡ ታዘው ፍቃደኛ ስላልሆኑ፣ በፓርቲው ደጋፊዎችና ገለልተኛ ኣቋም ያላቸው መምህራን ኣነስተኛ ግጭት ተፈጥሮ ትምህርትቤቱ ለኣንድ ቀን ተዘግቶ መዋሉ ታውቀዋል።

ኣምስት (ከወራት በፊት ነው) ኲሓ ኣከባቢ ነው። ኣስተዳዳሪዎቹ የገበሬዎችን መሬት ወደ ከተማ እንዲገባ ተወስነዋል በማለት ለመውሰድ ሲሞክሩ የገበሬዎቹ ተወካዮች “መሬታችን ኣንሰጥም፣ ወደ ከተማ ኣልገባም፣ ከገባ ግን እንዲገባ የተወሰነበት ሕጋዊ የኣስተዳደሩ ወረቀት ወይ ፕላን ኣሳዩን።” በማለት ተቃውማቸው ያሰሙ ሲሆን ተወካዮቹ ያለ በቂ ምክንያት መታሰራቸው ታውቀዋል።

ስድስት በእንደርታ ወረዳ የሚገኙ ኣርሶ ኣደሮች መሬታቸው በኢንቨስትመንት ስም ተነጥቀው ስርዓቱ ለሚደግፉ ባለሃብቶች እየተሰጠ ሲሆን ገበሬዎቹ ተደራጅተው ጉዳያቸው ለሚመለከተው ኣካል ቢያቀርቡም መፍትሔ እንዳላገኙ ጠቁመዋል። ማስፈራርያም እየደረሰባቸው ነው።

በመጨረሻ  በትግራይ ኣከባቢዎች ባደረግነው ፖለቲካዊ ተሞክሮ መሰረት (ስለ ኣብዛኛው ነዋሪ ቀለል ባለ ግምገማ መሰረት)
1) ለውጥ ፈላጊ: ኣላማጣ፣ ሑመራ፣ ተምቤን፣ ሽረ
2) ጥሩ የፖለቲካ ግንዛቤ ያለው (ለውጥ ለማምጣት ግን ቅስቀሳ የሚያስፈልገው): ውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ ኣክሱም፣ ማይጨው
3) በፍርሃት የሚኖር ህዝብ: እንደርታ፣ ሓውዜን፣ ዓድዋ
ባጠቃላይ በትግራይ ሙስና ሕጋዊ ስራ ‘የሆነበት ሁኔታ ነው ያለው’።  መርጃው የተወሰደበት ማጣቀሻ

ኣንድ ለኣምስት በህወሓት ጉባኤ: ‘የድርጅት ሥራ’ (ከመቐለ)

EMF – ትናንት ማታ ግርማይ ገብሩ (የVOAው የመቐለ ዘጋቢ ጋዜጠኛ) የህወሓት ስብሰባ ኣስመልክቶ ባጠናቀረው ዘገባ ብርሃነ ኪዳነማርያም የተባለ የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባል በህወሓቶች የመከፋፈል ኣደጋ ስለመኖሩና ኣለመኖሩ እንዲያብራራ ተጠይቆ ሁሌም እንደሚሉት ኣፉን ሞልቶ ‘በፍፁም የለም’ እንደ ሚል ኣልተጠራጠርኩም ነበር። ምክንያቱም መሪዎቻችን በ1993 ዓም ‘በህወሓት መከፋፈል ኣልነበረም’ ብለው የሚከራከሩኮ ናቸው። ደግሞ ኣደጋው ቢኖርስ እንዴት ለሚድያ ሰው ‘ኣዎ የመከፋፈል ነገር ኣለ’ ብሎ ሊናገር ይችላል? ግን ኣደጋው መኖሩ ኣልደበቀም ……. ‘ መከራከር ያለ ነው…. ምናምን …. ዙርያ ጥምጥም …. ። እኛስ ገብቶናል፤ እናውቀዋለንም።
የመሪዎቹ ኣለመግባባት በጉባኤውም እንደቀጠለ ነው። ስብሓት ነጋ ያለ ድምፅ እንዲሳተፍ ተደርገዋል። ሙሁራን (በተለይ ደግሞ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ኣባላት) ጥያቄ ሊያስነሱ ይችላሉ በሚል ስጋት በጉባኤው እንዳይሳተፉ ተደረገዋል (ሁለት ብቻ ያለ ድምፅ እየሳተፉ ነው)።

የትግራይ ቡድን (የነ ኣባይ ወልዱ ማለቴ ነው) ተሳታፊዎቹ በጥንቃቄ መመልመል ችለዋል። ከ40 በላይ ከሚሆኑ የፓርቲው ኣደረጃጀት ወረዳዎች (ከያንዳንዱ) 25 በድምፅና 1 ያለ ድምፅ በጠቅላላ ወደ 1500 የሚጠጉ ተሳታፊዎች ኣሉ። ኣብዛኞቹ ተሳታፊዎች ገበሬዎችና በብዛት የኣንደኛ ደረጃ ኣስተማሪዎች እንዲሆኑ ተደርገዋል (ጥያቄ እንዳያበዙ ተብሎ ነው)።

በጉባኤው ‘1ለ5’ የተባለ የፖለቲካ ስትራተጂ ተግባራዊ እየሆነ ነው። የተሳታፊዎቹ ኣቀማመጥ በየመጡበት መሰረት ነው። ኣምስት-ኣምስት ተበድነው ይቀመጣሉ። ለእያንዳንዱ ባለ ኣምስት ቡድን ኣንድ ታማኝ (በቤተሰብና ጎጥ መሰረት) መሪ ኣለ። እያንዳንዱን የቡድኑ ኣባል የተመደበለትን የቡድኑ መሪ ያዘዘውን ያደርጋል። ድምፅ በሚሰጥበት ግዜ ኣባላቱ የቡድን መሪያቸው ተከትለው እጃቸው ያወጣሉ። እሱ ዝም ካለ ዝም ይላሉ።
የጉባኤው መሪዎች (Presidium) ለተሳታፊዎች ዕድል ሲሰጡ (ተመራጮች ለመጠቆም ይሁን ሓሳብ ለመስጠት) ቀድመው ለማን መስጠት እንዳለባቸው፣ ቀጣዩ ባለ ተራ ማን እንደሆነና ማንን እንደሚጠቁም ወይ ምን ዓይነት ሓሳብ እንደሚሰጥ ያውቁታል። ሁሉም ነገር ተደራጅተዋል። (‘የድርጅት ስራ’ ነው)። በጉባኤው ማን እንደሚሳተፍ (እንደማይሳተፍ) በዝርዝር ተቀምጠዋል።

ለምሳሌ የጉባኤው ሰብሳቢዎች (Presidium) ሲመረጡ ‘የድርጅት ስራ’ ተግባራዊ ሁነዋል። ኣባላቱ የተመረጡት ባለፈው ሳምንት በተደረገው ‘የኣጀንዳ መለየትና ሽምግልና’ ስብሰባ ነው (ግን ጉባኤው ሲጀመር የተመረጡ ኣስመስለው ኣቀረቡዋቸው)። ኣመራረጣቸው ሁለት ከትግራይ ቡድን (የነኣባይ ወልዱ)፣ ሁለት ከኣዲስ ኣበባ ቡድን (የነ ደብረፅዮን ወይ ኣርከበ) ሲሆኑ ኣንድ ደግሞ ከመሃል ሰፋሪዎቹ እንዲሆን ተሰማምተው ነበር። ኣምስቱ የተጠቆሙት ባለፈው ስብሰባ ተካፋይ በነበሩ የማእከላዊ ኮሚቴ ኣባላት ናቸው። ሌሎች ኣይፈቀድላቸውም። በዚ መሰረት:
ከትግራይ ቡድን
1) ኣባይ ወልዱ (ከወንዶች)
2) ኣዜብ መስፍን (ከሴቶች)
ከኣዲስ ኣበባ ቡድን
1) ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ከወንዶች)
2) ፈትለወርቅ ገ/ሄር መንጀርኖ (ከሴቶች)
ከመሃል ሰፋሪዎች
ኣባይ ፀሃዬ ናቸው።

በድርጅት ስራው የኣዲስ ኣበባ ቡድን ግራ እንደተጋባና የኣቋም ልዩነቱ በግልፅ እንደሚንፀባረክ ለማወቅ ተችለዋል። የኣዲስ ኣበባዎቹ በጉባኤው ደስተኝች እንዳልሆኑ ያስታውቃሉ። ግን ጫና በዝተባቸዋል። “ህወሓት ጥንካሬ ከሌለው እኛ ምን ይዋጠን ?” የሚል ተማፅኖ ከሌሎች የኢህኣዴግ ኣባል ድርጅቶች ይሰማል።
የመቐለው ዘጋቢም በመጨረሻ እንዲህ አለ፡ “የመሪዎቻችን የምሽት ቆይታ፣ የስካር ነገር፣ የዩኒቨርስቲ ሴት ተማሪዎች ጉዳይ …… ብቻ ይደብራል። በመቀሌ በ14፣ 15 ና 16 ቀበሌዎች በወረዱ መጠጥ ቤቶች ጎራ በሉ። በምታዩት ነገር ትገረማላቹ። እኔ ግን ስለ ደበረኝ እዚሁ ልፅፈው ኣልቻልኩም። ብቻ ግን የመሪዎቻፍሁን ስነ ምግባር ብታውቁ ኑሮ ከኔ በላይ እንደምትቃወሙዋቸው ኣልጠራጠርም።” ምንጭ ማጣቀሻ

አገሪቱ የተጠመደችባቸው ውስብስብ ችግሮች!

ስለኢትዮጵያ በአጠቃላይ ምን ያልተባለ፤ያልተጻፈ አለ? ምን አዲስ ነገር ሊጻፍ ይችላል? ከሚሆሉ ነገሮች በስተቀር፤ ስለ አገራችን ያልተጻፈ ጉዳይ የለም። ሁሉም በየፊናው የተቻለውን ብሏል፤ጽፏል። አዲሱ፤ይህ መዘዘኛ ስርአት በየቀኑ እየፈለፈለ የሚያወጣቸው ፤የተደመሩና የተከማቹ፤ጊዜያቸውን ጠብቀው የሚፈነዱ የፖለቲካ ፈንጂውች እንጂ ሁሉም ተብሏል። አንድ ጉዳይ ግን እወነት ነው፤የሚጻፉ የተባሉ ሁሉ የተመሳሰሉ ቢሆኑም የቆሙበትንና የመፍትሔ ፍለጋ ላይ በአጽንኦም ተግባራዊነቱ ላይ ብዙ ፈታኝ ምእራፎች ተደቅነው ይታያሉ። 
 
የኢትዮጵያ ችግር አንድ ሁለት ተብሎ የሚዘለቅ አይደለም። ለዘመናት በተለያዩ ስርአቶች የተፍጠሩ፤የተከማቹና ውስብስብ ለመፍትሄል አስቸጋሪ የሆኑ ናቸው። 

ከዚህ በታች በጥቅሉ የተቀመጡ አሳቦች አዲስ ሳይሆኑ የነበሩ ናዘው። ለምን መጥቀስ አስፈለገ ቢባል፤ የጉዳዮቹን ፈታኝነትና የሚያመለክቱትን አደጋ አጢኖ ግንዛባ ለመውሰድ፤ ብሎም መፍትሄ ለማፈላለግ ቢረዳ ተብሎ ነው። የተዘረዘሩት ባመዛኙ ስርአቱ የፈጠራቸው፤ያገነናቸው ቢሆኑም፤ በቅድሚያ ስርአቱ፤ ያለፉት ስርአቶች፤አጎራባች አገሮች፤አለማቀፍ ሁኔታዎችና፤ ሳይጠቀስም መታለፍ የማይችሉት በጅምላ በተቃዋሚነት የተሰለፉ ባገርም፤በውጭም፤በሰላምም፤ባመጽም የሚታገሉ የተሰባሰበውና የተበታተነው ሐይሎች ጭምር ናቸው። ብዙ የማያናቁሩም ባይሆኑ፤ በየፈርጃቸው መጠቃልለ ያለባቸውም ቢመስልም፤ ለመቃኘት ያክል አሉ የሚባሉ ፈታኝ ምስቅልቅሎቻችን ምን ይመስላሉ።

1. ዘረኝነትና መዘዙ፤
በአይነታቸው አስከፊ ከተባሉት በደቡብ አፍሪካና በሌሎች አካባቢ ከታዩት ባልተናነሰ፤እንዲያውም አገር በቀል በመሆኑ የከፋ ያንድ አናሳ ዘር የበላይነትና ጉዳዮችን በራሱ የስልጣን ጥምና ጥቅም ዙሪያ እያሽከረከረ በአሁኑ ወቅት ፈታኝ ችግሮችን ደቅኗል። ያለው እንዳለ ሆኖ የሚያመጣውና፤ እያመጣ ያለው መዘዝ በቀላሉ ለመወጣት የሚቻል አይደለም። ስር ሰዶ፤ፍሬ አፍረቶ ውጤቱ በሕዝቦች መካከል አለመተማማን፤መቃቃር፤ መጋጨት፤መፈናቀልን ፍጠሮ ጉዳዩ አሳሳቢ ሂኔታ ላይ ደርሳል። ዘለቄታውስ ምን ይሆን ብሎ መጠየቅ ተገቢ ቢሆንም፤ ማንም መገመት እንደሚችለው እትዮጵያ እንደአገር ልትቀጥል የምትችልበትን መሰርት ያናጋና አደጋ የደቀነ አብይ ችግር ሆኗል። በነጻንተ ከሚገኝ አንድንት ይልቅ የጠመንጃ ሐይል ፊት ካሰከተለው የተለየ ውጤት የለውም። ሌሎቹ ያገር ችግሮች ይህን ለበለጠ ጥፋት ይመግቡታል እንጂ አይቀርፉትም።

2. የመልካም አስተዳዳር እጦት፤
ያለው ስርአት ሁሉንም የፖለቲካ፤ የኢኮኖሚ፤የማህበረሰብና በሐይማኖት ሳይቀር አጠቃላል የአስተዳደር እርከኑንና አስከ ቤተሰብ ድረስ ዘልቆ በማፈን ህዝም እንዳይናገር፤እንዳይጽፍ፤ እዳይሰበሰብ፤ በነጻነት እናዳያመልክ ጠፍሮ ቀፍድዶ አደንዝዞ በገዛ አገሩ ባይተዋር የበዬ ተመልካች አድርጎት ለመዝለቁ የሚያጠያይቅ አይደለም። አገሪቱ በተከታታይ የሶስት ስርአቶች የንጉሥ፤ያምባገንንና የዘረኛ ስርአት ሰለባ ሆና ሕዝብ መከራውን ሲጋት፤ አገር ስትፍርስአ፤ አንድነት ሲሸረሸር፤ ጥፋት ሲመርት ለማየት በቅተናል።

3. ድህነት፤
ዛሬ አትዮጵያ ብዙዎች የሚራቡባት፤ ሉሮ ያሸቆለቆበባት፤ ድህነት አገርንና ህዝብን የአለም ጭራ ያደረገበት ደረጃ ላይ ደርሳለች። በአንዳሩም ጥቂት ባስተዳደር እርከኑ ላይ የተንጠላጠሉ አናሳውና አጋፋሪዎቹ ሀብት አካብተው ትላንት የመጡበትን ብቻ ሳይሆን ነገ የሚሄዱበትን እጣ ፍንታቸውን ለማየት የተሳናቸው አዲስ የበላታና ቡድን መፈጠሩ ነው። አብረን ሠርተን አብረን እንጠቀም ሳይሆን ሊሠራ የሚችለውን እጅ የሚያስር፤ አቅም ያለውን የሚያመክን የስግብግቡችን ጥርቅምን ፈጥራል። ድህነት የችግሮች ሁሉ መሰረት ነው። የህዝብ ድህነት ሲንር ዝም ከማለት ባሸገር አመጽን፤ ምንም ማንም ሌያግደው የማይችለውን ማእበል ይወልዳል። በመሥራት ማደግ መበልጽግ ሲቻል በዝርፊያ ድሀ፤የድሀ ድሀ ያደረጉት ተጠያቂዎች ናቸው። ያገሪቱን ሀብት የተፈጥሮ ለም መሬተና ማእድናቱን ባልባሌ አስተዛዛቢ፤ሚዛን በጎደለው አስተሳሰብ ለባእድ አሳልፎ መስጠት ወንጀል፤ ያገር ክህደት የከፋ ወንጀል ነው።

4. ዝረፊያ - ኪራይ ሰብሳቢ ስርአት(ኮረፐሺን)፤
ምንጩ ከደፈረስ የጠራ ውሀ የለም። በአገሪቱ ዝርፊያ አይን ያወጣ ሙሰኝነት፤ ጥቅምን ማግበስብስ ፤ ያገሪቱ ሀብት በተለያየ መልኩ በሚታይና በማይታይ ስልት ወደ ውጭ እየጎረፈ ለመሆኑ፤ ከድሀ አፍ እየተነጠቀ ለመንጎዱ ብዙ ዋቢዎች በይፋ እየቀረቡ ይገኛሉ። ሕዝብ ይህን አያውቅም አይሰማም አረዳም፤ የመስሚያ የመረጃ አውታሮች ሁሉ ታፍነው ህዝብ የራሱ ጉዳይ ባይተዋር ሆኗል። በቀላሉ አደንዝዘውታል። ኪራይ ሰብሳቢነት ሌላ ትርጉም አያሻውም፤ ስርአቱን በማፈኛነት በመጠቀም መበልጸግ ብቻ ነው። በቀላሉ አይን ያወጣ እፍረት የጣ ዝርፊያ። የአገሪቱ ኢኮኖሚ የሚንቀሳቀሰው ባንጋፋ በስርአቱ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችና በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች መሆኑ የሚያሳዝንና የሚያሳፍር ተግባር ነው። በሰርአቱ ስር የተሰገሰጉ፤ጊዜ የሚገልጣቸው የማይመስላቸው ከተጠያቂነት ማምልጥ አይችሉም። በንጽህና መበልጸግ አለ፤ በዝርፊያ ግን በማንናቸውም መልኩ ያስጠይቃል። ከሁሉም የበለጠ ሓጢአት ነው። እግዚአብሔር ድሃ ሲያለቅስ አይወድም። ስላላመኑም ከቅጣት ማምለጥ የለም።

5. የሀይማኖት ነጻነት መጥፋት፤
አደጋውች በየፈርጁ ተኮልኩለዋል። የተደማመሩ ቀውሶች መዘዛቸው የከፋ ነው። ጳጳስ ፈንቅሉ የእምነት አውታሩን ከመቆጣጠር፤ የእምነትን ህገደንብ ለውጦ ሌላ እምንት ፍጥሮ፤ባማኙ ላይ መጫን፤ ለስልጣን፤ ለጥቅም ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት ነው። ገዳመት ተገለበጡ፤ ንጹህ አባቶቻችን ተዋከቡ፤አለቀሱ፤ተሰደዱ፤ለመከራ ተዳረጉ። በእምነት ጣልቃ ገብነት መዘዙ፤ ይህ ተፈጥሮ ያመጣችው ነው ተባለም አልተባለ፤ከላይ የመጣ መአት ሊፈስ ይችልል። ለተረዳውም የሆነውን አይተናል። በሌላ መልኩ፤ ተስማምቶ ተከባብሮ ባንድነት የኖረውን ሕዝም ፈተና ውስጥ ከቶታል። ከግፊትም ብዛት ሰላማዊውን ሕዝም ወደ አላስፈላጊ ጎዳና ይመራዋል፤ አመጽም ይባል ሽብር ይቀፈቅፋል። በዚህም ሆነ በዚያ እሳት ይጭራል፤ እልቂት ይጋብዛል። ጠመንጃም ሊየግደው የማይችል የሕዝብ ማእበልን ይወልዳል።

6. አካባቢ አጎራባችና ተዛማችች፤
ለችግሮቻችን መፍትሄ ሳይሆን እሳቱን ጭድ የሚመግቡ ሀይሎች ብዙ ናቸው። ኤርትራረ የሰበሰበቻቸው በአብዛኛው አገርን አንድነት የሚያናጉ ሀይሎች ከዚሁ ይመደባሉ። የተዳፈነ እሳት ይምስል እንጂ ቀውስ ሲመጣ እነዚህ ሀይሎች በአራቱም ማእዘናት እሳት የሚያነዱ የተደቀኑ አደጋዎች ናቸው። ኤርትረም ለኤትዮጵያ ሳይሆን ለረሷ ደህነት፤ በከፊልም የቂም መወጫ መንገዷ እንደሆነም መዘንጋት የለበትም። ከውጭ የሚርገበገቡ ሽብርተኝነትን የሚቀሰቅሱና የሚመግቡ ሂደቶችም ሌላዎቹ ችግሮች ናቸው። የግድቡ ውጥንቅጥም አንድ እራሱን የቻለ ፈተና ነው:፡ አባይ መገደቡን፤አገር መልማቷን፤ ሕዝብ መበልጸጉን የሚጠላ ኢትዮጵያዊ የለም። ጥያቄው ልማት ከማን እጅ እንዲትና ለማ የሚሉት ናቸው። ያገሪቱን የአመት በጀት በሚያክል ንዋይ፤ ግዝፈቱ ለፍጻሜው አደጋ የሚጋብዝ ትልም፤ ከአካባቢውና አጎራባች አገሮች ጋር ለዘለቄታው የሚያፋርስ፤ ጦርነትን የሚጋብዝ የልማት ትልም ለሁሉም ፈታኝ ነው። ይህ አገርን የመውደድና የመጥላት ጉዳይ አይደለም ያገር የዘላቂ ደህንነት እነጂ።

7. የምእራቡ ትጽእኖ፤
ምስራቡን በእጅጉ ታዝበነዋል። ለነገሩ ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ የሆነ ነገር። የሕዝቡን ጥቅም መብትና ነጻነት፤ ያገሪቱን ደህንነት ወደጎን በመተው ከሟቹ ጋርና አሁንም አንድ በመሆን፤ከመፍትሄ ይልቅ ለሕዝብና ለአገር ስቃይ መራዘም አስተዋጽኦ መሆኑ አሌ አይባልም። ይባስ ብሎ በበለጠ ሊያስደንግጣቸው በሚችል ሁኔታ አሁን የሚታየው የሐይማኖት ማእበል፤ የበለጠ የሚያሰጋቸው፤ ስርአቱን ይበል የሚሉበትን ሁኔታነ የሚጋብዝ ለው። ምእራቡ ከፊቱ የበለጠ ምእራብ ሆነ ማለት ይቀላል። ዲሞክራሲና ለሕዝብ መብትም መቆርቆር ካባ ልምስ እንጂ ጥቅም ቅዲሚያን ይዛ ነጉዳለች። ዘመኑም የከፋ ነው!!!!

8. የተቃዋሚው አካሄድ፤
እንግዲህ አልቀሬ! ከየትኛው ቡድን! እንበላ። ከችግሩ ወይስ ከመፍተትሔው? ስርአቱ-በአመዛኙ፤ሊሎችም ተጠያቂ ቢሆንም፤ ተቃዋሚው መፍትሔ ለመሆን በሚያደርገው ጥረት ለችግሮች እይተኛ አስተዋጽኦ መሆኑ ሳይወጠቀስ ሊታለፍ አይገባም። የተቃዋሚው ችግር አንድና አንድ ብቻ ነው። መሰባሰብ በአላማና በመርህ ባንድ ላይ አለመሆን!!!! ሌላ ላይደለም፤ጂኦግራፊም አቅምም ሌላም ሌላም ቢጠቀስ፤ ሕዝብን የሚአክል ሃይል፤ አገርን የሚያክ ጉዳይ ይዞ መዘናጋት ድክመት ብቻ ሳይሆን አተጠያቂነት ውስጥ መመደቡ አይቀሬ ነው።
ታዲያ፤ኢትየጵያ ይህን ሁሉ፤ ከዚህም በዘተረፈ ያልተጠቀሱ የዘማናት ፈተናዎችን ቀፍቅፋ ታቅፋለች። ተሸፋፍኖ መተኛት ችግሮችን አያጠፋም፤ ያባብሳል እንጂ። እስካሁን በእያንዳንዱ አእምሮ ውስጥ መፍትሔ የሚል ደወል መቃጨሉ አይቀርም።
ምፍትሄው በቅድሚያ ካለው አስተዳደር፤ ከምእራቡና ከሌሎች አይገኝም። መፍትሔው ያለው ከሕዝቡና ፋና እያበሩ፤ ፈር እየቀደዱ አቅጣጫን በሚሰጡት፤በሚጠቁሙ ልጆቹ እጅ ነው። 


ገና በጥዋቱ፤ በደርግ ጊዜ ማለት ነው፤ ገበሬው ከገጠር ዱላውን የሽቅብ እየዶለ ሆ!ሆ!ሆ! እያለ አደባባዩን በሞላበት ወቅት፤ አንድ የውጪ ዜጋ "ይህ ሁሉ ዱላ ወደጠመንጃ ሳይለወጥ እግራችሁን አውጡ" ብሎ በአገር ጋዜጣ ጽፎ ነበር፤ ወገኖቹን ማለቱ ነው። ሐቁ ይኸው ነው፤ የያዘን አባዜ ቀላል አይደለምና ምሳሌው ሁሉን ይናገራል። አገሪቱ ድህንተ የለባትም፤ሁኔታዎች አደኸይዋት እንጂ። የሰው-በያይነቱ፤የተፈጥሮ ሓብት ባለጸጋ ናት። ይህ ሆኖ ሳለ፤ ለዚህ ሁሉ ቀዳሚ መፍትሔ የሚሆነው መልከም አስተዳደር መሆኑ አይዘነጋም። መሰባሰብ ማሰባሰቡም ለዚሁ ነው። ስልታጣንም፤ የመልካም አስተዳደር ባለበት ማለት ነው፤ ከህዝም እንጂ፤ ከእንግዲህ አገሪቱም፤ሕዝብም፤ ጊዜውም ሌላ የጥፋት ስርአት አይፈልጉም። ሁኔታዎችን እንደነበሩ እንዳሉ በመርገጥ መቀጠል የጤንንት ምልክት አይደልመ። ጥቅምም፤ጊዜም፤ሰውም ያልፋሉ፤ አገርና ትውልድ ይቀጥላሉ። ይህ ሁሉ ሲያልፍ ለአድራጊዎች የሚሰጣቸው ስም ምን ይሆን? ጊዜ ምስክር ትሁን-ካለች ማለት ነው።

ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር፤በሕዝቧና በሓቀኛ ልጆችዋ ትድናለች! 

 ቸር ይግጠመን!!
ፍ.አ.
03 13 13

Tuesday, March 19, 2013

Ethiopia ‘blocks’ Al Jazeera websites


 China expels Al Jazeera correspondent

Traffic to English and Arabic websites has plummeted since the network aired coverage of protests in August last year.
Last Modified: 18 Mar 2013 14:40
Traffic to English and Arabic websites has plummeted since the network aired coverage of protests in August last year. Al Jazeera’s English and Arabic websites are reported to have been blocked in Ethiopia, raising fresh fears that the government is continuing its efforts to silence the media.

Though the authorities in Addis Ababa have refused to comment on the reported censorship, Google Analytics data accessed by Al Jazeera shows that traffic from Ethiopia to the English website had plummeted from 50,000 hits in July 2012 to just 114 in September.

Traffic data revealed a similar drop for the Arabic website, with visits to the site dropping to 2 in September from 5,371 in July. A blogger, who cannot be identified for his own safety, said Ethiopian censors had been targeting Al Jazeera since the Qatar-based network began airing coverage of ongoing protests against the way in which spiritual leaders are elected in the Horn of African nation.

The steep decline in web traffic began on August 2 last year, the same day that Al Jazeera Mubasher aired a forumwith guests denouncing the government’s “interference” with Muslim religious affairs, and three days after Al Jazeera English published an article detailing deadly ethnic clashes between two of the country’s southern tribes.

Attempts by Al Jazeera to get an official response from authorities failed.
Poor track record Ethiopia is ranked 137 out of 179 surveyed nations on the latest Press Freedom Index of Reporters Without Borders (RSF), an international advocacy group for press rights.

Both RSF and the Committee to Protect Journalists (CPJ) have tied Ethiopia’s deteriorating media environment, in part, to a 2009 anti-terrorism law that has been used to jail 11 journalists since its ratification.

“The usage and practice of this law is illegal. It has a clause that makes whoever writes about so-called terrorist groups, which are mostly normal opposition groups, a terrorist,” CPJ’s East Africa Consultant Thom Rhodes told Al Jazeera. “Now it’s got to the point that the law is being used to label those in the Muslim community conducting peaceful protests to defend their right to choose their spiritual leaders as terrorists. It’s a sad state of affairs.”

CPJ says Ethiopia is the second-highest jailer of journalists in Africa after neighbouring Eritrea, were seven journalists are currently detained.
Both the RSF and CPJ have expressed concern over reports that the country has begun using much more sophisticated online censorship systems over the last year, including ones that can identify specific internet protocols and block them.
Since Ethiopia’s government owns the sole telecommunications provider in the country, Ethio Telecom, it allows authorities to tightly control internet freedom. http://ethioforum.org/ethiopia-blocks-al-jazeera-websites/

የታሰሩት ሰልፈኞች ተፈቱ (ፎቶ እና የእስር ቤት ውሎ ዘጋባቸውን ይዘናል)

(በበፍቃዱ ኃይሉ)
EMF – መጋቢት 8/2005 የባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሺስት ጣሊያን ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት (በጣሊያን አገር፣ የትውልድ መንደሩ አካባቢ) መቆም በመቃወም የሰልፍ ጉዞ ከስድስት ኪሎ (የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ኀውልት) እስከ ጣሊያን ኤምባሲ ድረስ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነበር፡፡ የሰልፉ ተሳታፊዎች ከጀርባው ላይ ‹‹ለግራዚያኒ ኀውልት ማሠራት አባቶቻችን የከፈሉትን መስዋዕትነት ማራከስ ነው›› የሚል ጽሑፍ የታተመበት ቀይ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር፡፡ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ደግሞ ‹‹ይቺ ባቄላ…›› በሚል ምክንያት ነው መሰለኝ ‹‹የተቃውሞ ሰልፍ…›› የሚባለውን ነገር ለማስቆም ራሱ ግብግብ ፈጠረ፣ ወጣቷ ዓለምን የቀን አጋጣሚ ስድስት ኪሎ አካባቢ፣ በዕለተ እሁድ (መጋቢት 8/2005) አንቀዥቅዦ አመጣት፡፡ የለበሰችው የአዘቦት ቀይ ቲ-ሸርት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለመዋል ምክንያት ይሆነኛል ብላ አልተገመተችም ነበር፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ቀይ ለባሾቹን ማፈስ ሲጀምር ዓለምንም አብሮ አፍሶ አጋዛት፡፡

ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር
ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር


በተመሳሳይ ሰዓት ለሥራ ጉዳይ ጓዙን ጠቅልሎ ወደአፋር ለመጓዝ እየጠበቁት ያሉ ባልደረቦቹን ለማግኘት በታክሲ ውስጥ ይጓዝ የነበረ አንድ ሰው ከስድስት ኪሎ ተነስቶ አምስት ኪሎ እስኪደርስ የተመለከተውን ሁካታ ዓይቶ ላለማለፍ ከታክሲ ይወርዳል፡፡ ፖሊሶች ከሰልፈኞቹ ውስጥ አሳደው የያዙትን እያፈሱ መኪና ውስጥ ሲያጉሩ፣ ከፖሊሶች ዕይታ እየተሰወረ በሞባይሉ ፎቶ ለማንሳት ሲሞክር፣ አንድም የረባ ፎቶ ሳያነሳ በሦስተኛው ፎቶ ላይ ከፖሊሶች ጋር ዓይን ለዓይን ተጋጠመ፡፡ እሱም ተይዞ ተከተላቸው፡፡ ይህ ድንገተኛ እስረኛ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ሆነ፡፡ የታፈሱት ሰልፈኞች ሁሉ የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር፡፡ ጊቢው ውስጥ እንደደረስኩ ከፊት ለፊቴ ደረጃው ላይ የተኮለኮሉትን ሰልፈኞች ተመለከትኩ፡፡ ወጣቶቹ ታፍሰው የገቡ ሳይሆን ወደው የተሰበሰቡ ይመስሉ ነበር፡፡ እንዲያውም በገባሁ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ጮክ ብለው ይዘፍኑ ጀመር፡-
‹‹… ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም፣ ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም…››


በዚህ ጊዜ ከፖሊሶቹ አንዱ አብሮ ሲዘምር ይታይ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ የተሻለ ትሁቶች ቢሆኑም፣ ሲቪል ለባሾቹ ግን ማመናጨቅ እና ማዋከብ ዋነኛ ሥራቸው ነበር፡፡ እኔን በመኪና ይዘውኝ ከመጡት ውስጥ አንዱ ‹‹ዴሞክራሲ በዛ…›› የሚለውን ቃል እየደጋገመ በቁጭት ይናገራል፡፡ ብዙዎቹ የመምሪያው ፖሊሶች ከየት እንደመጣ የማያውቁት ኮማንደር ግን የተቆጨው በመዘግየቱ ነው፤ ‹‹ይሄን ያክል እስኪሰባሰቡ መቆየት አልነበረብንም›› አለ – እኔው ጎን ቁጭ ብለው ሲነጋገሩ፡፡ በሬዲዮናቸው ሲለዋወጡ ከነበረው ውስጥም ‹‹ሱማሌ ተራ የተጎዳውን ሰውዬ የት ወሰዳችሁት?… ተክለሃይማኖት ሆስፒታል?…›› ይባባሉ ነበር፡፡ በዚሁ ጉዳይ ይሁን አይሁን ግን ‹‹መረጃም (ማስረጃም)›› አልነበረኝም፡፡


ጊቢው ውስጥ ከሌሎቹ እንዳልቀላቀልና ብቻዬን እንድቆይ አድርገውኛል፡፡ ባንድ በኩል ስልኬ ላይ ያሉትን ፎቶዎች አጥፍተው ይፈቱኛል፣ ጉዞዬም ይቀጥላል በሚል ደስ ብሎኛል፡፡ በሌላ በኩል በዓይን የማውቃቸውን እነዚያን ልጆች ቀረብ ብዬ አለማነጋገሬ ቆጭቶኛል፡፡ በዚህ መሐል ግን ሁሉም እየሄዱ ቃል ሲሰጡ ቆዩ (ቃል ሲባል ቃል እንዳይመስላችሁ፤ ከስም አንስቶ የኔ የምትሉትን ነገር በሙሉ ይጠይቋችኋል)፤ ከዚያም የኔም ተራ ደረሰና ቃል ሰጥቼ ሳበቃ እኔም በቀላሉ እንደማልሰናበት ሲያረዱኝ የጓዝ ኮተቴን ሁሉ አስመዝግቤ እዚያው ተጠቃለልኩ፡፡
ከዚያም ቃል የመስጠቱ ሥነ ስርዓት ቀጠለ፤ የመጣው ሁሉ በራሱ መንገድ ያንኑ ጥያቄ መልሶ፣ መላልሶ እያንዳንዱን ታሳሪ (ተጠርጣሪ ልበል ይሆን?) ይጠይቃል፤ እያንዳንዱም ተጠርጣሪ ይመልሳል፡፡ ሆኖም ብዙዎቹን መርማሪዎች የብስጭት መንስኤ የሚሆን ነገር ባለራዕዮቹ ወጣቶች ሳይናገሩ አይወጡም ነበር፡፡ ብሔር ሲባሉ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ይላሉ፡፡ ይህንን የሚሉት ‹‹ብሔር›› የሚለው ቃል ከግዕዝ የተወሰደ ሲሆን፣ ትርጉሙም ‹‹አገር›› መሆኑን እያጣቀሱ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አባባል ለመርማሪዎቹ የሚያበሳጭ ድፍረት ነበር፡፡
ፖሊሶቹ የሆነችውን ሁሉ እየደወሉ፣ ለአለቆቻቸው ይናገራሉ፡፡ ከዚህ መሐል ከሰልፈኞቹ አንዱ ለብሶት የነበረው ባንዲራ ላይ በእስክርቢቶ የጻፈውን ደብዳቤ ከስልኩ ወዲያ ላለ ሰው በንባብ ሲያጽፉት ሰምቻለሁ፡፡ ጽሑፉ ባብዛኛው መንፈሳዊ ነው ቢባል ይቀላል፡፡ ‹‹ለእመቤታችን በአስራትነት የተሰጠችው አገራችን ኢትዮጵያ…›› ብሎ ነው የሚጀምረው፡፡


ምርመራው/ጥያቄው ቀጥሏል፤ ከጠያቂዎቹ መካከል የደኅንነት እና የኢንሳ ሰዎችም ነበሩበት፡፡ ከጥያቄዎቻቸውም ውስጥ የኢሜይል አድራሻ እና የይለፍ ቃል፣ የፌስቡክ አድራሻ እና የይለፍ ቃልም ይጠይቁ ነበር፡፡ እያንዳንዱ ታሳሪ (ተጠርጣሪ አልልም) ስሙን በቪድዮ ካሜራ ፊት እንዲናገር ይገደድ ነበር፡፡ እንግዲህ ይህንኛው መጀመሪያ ላይ እያንዳንዱ ሰው ከተነሳው ፎቶ በተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ የጅምላ እስር ውስጥ ካስተዋልኳቸው ጉዳዮች ውስጥ የሴቶቻችንን ጀግንነት ነበር፡፡ ለምሳሌ፣ እኔ ያለምንም ማንገራገር ምስሌን አስቀርጬ ወደቃለመጠይቁ ሳልፍ የሰማያዊ ፓርቲዋ አመራር አባል ሐና ዋለልኝ ‹‹አልቀረጽም፣ አሻፈረኝ›› ብላ ስትሟገት ድምፅዋ ይሰማኝ ነበር፡፡


ሲመሽ ይፈቱን ይሆን? እዚሁ ያሳድሩን ይሆን? ሌላ ቦታ ይወስዱን ይሆን? ምን ብለው ይከሱን ይሆን? እየተባባልን የተሰባሰብንባት አንዲት በረንዳ መሳይ ክፍል ውስጥ፣ ኢቴቪ በቀጥታ የሚያስተላልፋቸውን የአዳማ እና የመቐለ የኦሕዴድ እና የሕወሓት ስብሰባዎች መኮምኮም ጀመርን፡፡ አሳሪዎቻችንም በስልክ አለቆቻቸውን እያነጋገሩ ሽር ጉዳቸውን አጧጡፈውታል፡፡ ኢቴቪም ብቻውን በዓሉን ማክበር አልቻለም፡፡ መብራቱ ብልጭ ድርግም አበዛ፡፡ ብልጭ ድርግም አልኩ እንጂ ያበዛውስ ድርግም ማለት ነው፤ አልፎ፣ አልፎ ግን ላፍታ ብልጭ እያለ ነበር፡፡ በጨለማው ውስጥ ራታችንን በጨለማ ተቋደስን፡፡ ሁላችንም ምሳ ያልበላን ቢሆንም አንዳንዶች ግን ቁርሳቸውንም አልበሉም፡፡


የመታሰራችን ዜና በማኅበራዊ አውታሮች በመጠኑ ቢስተገባም የብዙዎቻችን ቤተሰቦች ግን አልሰሙም፤ ደውሎ የማሳወቅ ዕድሉም አልተሰጠንም፡፡ እዚያው ጨለማ ውስጥ ከቆየን በኋላ ወደ 3፡00 ሰዓት ገደማ ወደ ጃንሜዳ አካባቢ የሚገኝ ማረሚያ (እስር ቤት) በሁለት ዙር ተወሰድን ከ30 በላይ እስረኞች አንድ ላስቲክ ብቻ ወለሉ ላይ የተነጠፈበት ክፍል ውስጥ ብንታጎርም በእርስ በርሳችን ጫወታ ተጠምደን ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ እኛ ወደዚህ እስር ቤት ስንዛወር ቀይ ለባሽዋ ዓለም ተለቅቃ ወደቤቷ ሄዳለች፡፡) የሄድንበት በሰልፉ ዋዜማ ሲቀሰቅሱ ከታሰሩ ሌሎች ጋር ተቀላቅለናል፡፡ የጅምላ እስሩ ጉዳይ በዋዜማው እንደተጀመረ ያወቅኩትም ያኔ ነው፡፡ ቀድመው ከታሰሩት ውስጥ ሁለቱ ክፉኛ ቡጢ እና ካልቾ ቀምሰው እንደሆነ ለማወቅ እስኪናገሩ መጠበቅ አያስፈልገንም ነበር፤ የአንደኛው ጃኬት የደረቀ ደም ከፊትለፊት ይታይበታል፡፡


ለአምስት ሰዓት ዐሥራ አምስት ደቂቃዎች ሲቀሩት ግን እንደገና እንድንንቀሳቀስ ተነገረን፡፡ ከኛ ቀደም ብለው ሴቶቹም ወደቀጨኔ (ችሎት መድኃኔዓለም ኮንዴሚኒዬም አጠገበ ያለ) ወረዳ 9 ማረሚያ ቤት እንደተወሰዱ እና ከኛም ውስጥ 12ቶቻችን መከተል እንዳለብን ተነገረን፡፡ እዚያ እንደደረስን ግን ምነው እዚያው በቀረን የሚያስብል ትዕይንት ገጠመን፡፡ እያንዳንዱ ክፍል እላይ በላይ ተደራርበው በተኙ እስረኞች ተጨናንቋል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጫማ ማስቀመጫ ቦታ እንኳን በክፍሉ ውስጥ ስለሌለ ጫማዎቻችንን ውጪ እያስቀመጥን እንድንገባ ተገደድን፡፡ ሦስቱ (አራት ሜትር በአራት ሜትር የሚገመቱ) ክፍሎች ውስጥ አንዱ 37፣ አንዱ 34 እና ሌላኛው ውስጥ 30 እስረኞችን ይዟል፡፡


እንዳጋጣሚ 30 ሰዎች የያዘው ውስጥ ነበር እኔ የደረሰኝ፡፡ የኛ ክፍል ይሻላል ተብሎ ዶ/ር ያዕቆብንም አመጧቸው፡፡ ጉዳዩ በጣም አሳዛኝ ነበር፡፡ እኛስ ባልደከመ ጉልበታችን እንችለዋለን፤ ለርሳቸው ግን በጣም ፈታኝ እንደሚሆን መገመት ቀላል ነው፡፡ ክፍሉ በጣም ጥቅጥቅ ብሎ ከመሞላቱ የተነሳ ለኛ ቦታ ለማግኘት የቤቱ ካቦ ተነስቶ እያንዳንዱን እስረኛ እየቀሰቀሰ ማጠጋጋት ነበረበት፡፡ በቦታ ጥበት ምክንያት ደረቁ ወለል ላይ በአንድ ጎናችን እንድንተኛ ከመገደዳችን የተነሳ እኔ ይህን ጽሑፍ እስከምጽፍበት ሰዓት ድረስ ቁርቋሬው የፈጠረው ሕመም ጎኔን አያስነካኝም፡፡ ካቦው አጠጋግቶልን ሲጨርስ ሁላችንንም የገቢ ገንዘብ ተቀበለን እና ተኛን፡፡ እዚያ ክፍል ውስጥ መተኛት ማለት፣ መተኛት ማለት አይደለም፡፡ የክፍሉ መታፈን እና አስቀያሚ ጠረን፣ ሙቀት፣ በዚያ ላይ እየተቀባበሉ የሚያጨሱት ሲጃራ ጢስ፣ ከዚያ እና ከዚህ የሚተኮስ የፈስ ሽታ… ብቻ የአበሳ ናሙና ነበር፡፡ ሌሊቱን ሲዘንብ ማደሩ ግን በከፊልም ቢሆን የክፍሉን አየር አቀዝቅዞታል፤ ችግሩ ዝናቡ ውጪ ያስቀመጥነው ጫማ ውስጥ ውኃ መሙላቱ ብቻ ነበር፡፡


እንደምንም ነጋልንና ወደፍርድ ቤት እንደምንሄድ ተነግሮን ጥንድ ጥንድ እየተደረግ በካቴና ተቆላለፍን፡፡ ከመሐከላችን አንዱ የማኅበሩ አባል፣ ፀጉሩን አጎፍሮ ስለነበር (ለፍርድ ቤቱ ውበት አይመጥንም ብለው ይሆናል) ይቆረጥ አሉና መቀስ አንስተው ይከመክሙት ጀመር፡፡ ፀጉሩን ቆርጠው ሲጨርሱ አሰለፉንና ካቴናችንን ፈቱት፡፡ ‹‹ፍርድ ቤት መወሰዳችሁ ቀርቷል፣ ምናልባት ፖሊስ ጉዳዩን ይፈታዋል›› ተባልንና ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወደጃንሜዳ ማረሚያ ቤት መልሰው ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ለፖሊስ ዋስ እያቀረብን እንድንፈታ ተፈቀደልን፡፡ ቀድሞውንም የታሰርነው ያለወንጀል በመሆኑ አስገራሚ ውለታ አልነበረም፡፡

የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስፈልገው ቅድመ ሁኔታ ለመስተዳድሩ ማሳወቅ ሲሆን፣ መስተዳድሩ ደግሞ በ24 ሰዓት ውስጥ ‹‹አይሆንም›› የሚል ደብዳቤ ካልጻፈ እንደተፈቀደ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ሰልፍ ማድረጉ ሕጋዊ ስህተት የለበትም፣ ጉዳዩ ባንድ ጀምበር የተወለደ ሳይሆን ጋዜጦች ዜና የሰሩለት፣ ቁጥቦቹ ሬድዮዎች ሳይቀሩ ያወሩለት ጉዳይ ስለሆነ ወንጀል ነው ፍርድ ቤት ሊያቀርቡት አይችሉም/አይገባቸውምም፡፡ ነገር ግን ‹‹…ካፈርኩ አይመልሰኝ…›› ይመስላል በዋስትና እንድንፈታ ፈቅደው ያገቱብንን ንብረቶቻችንን እየመለሱ መጋቢት 9/2005 እኩለ ቀን ላይ አሰናበቱን፡፡

Monday, March 18, 2013

“Hands off our leader” Afar warriors warned Ethiopia’s minority junta

The Horn Times Newsletter 17 March 2013
by Getahune Bekele, South Africa

*popular cleric still in Semera ignoring threat of arrest

Afar warriors warned Ethiopia’s minority junta.Despite demonstration in tyrannized nation where adhering to Islam is becoming dangerous and hedged with restrictions under the controversial anti- terrorism law, the peaceful Islamic revolution is expanding and intensifying in Ethiopia much to the Frustration of the ruling TPLF junta.

The use of brute force as it was seen in the southern strategic city of Shashemene on Friday March 15, 2013 during a nationwide strike is not bringing the desired result of silencing the severly oppressed Ethiopians.
On Tuesday 12 March 2013,   the year-long struggle for religious freedom reached a millstone when one of Ethiopia’s colorful Muslim tribes, the Afar, officially joined the national movment.

After rumors spread like wild fire that the minority junta of Ethiopia was amassing troops near the key desert town of Semera, the principal center of Islamic learning and propagation, to arrest Afar’s most venerated religious leader, the honorable sheik Mohammed Awal Hayytan, the battle hardened traditional Afar warriors blocked the high way between the port of Djibouti and Ethiopia in peaceful protest on Tuesday afternon 12 March 2013 and again on Wednesday, triggering panic in Addis Ababa and other parts of Ethiopia.

According to eye witnesses, hundreds of stranded heavy tracks were allowed to leave the Afar towns of Mille and Adaitu on Wednesday evening without a shot being fired. But the situation remains tense.

“Sheik Mohammed Awal Hayytan is not a firebrand cleric with extremist views. He is a peaceable, gentle and modest preacher who always calls on all Ethiopians to unite. Ethiopiawenet had been synonymoys with generation of Afar clerics and sheik Hayytan is no different. Unfortunately talking about Ethiopiawenet is a crime punishable by death under the current brutal ruling junta. That is why they want his head on silver platter.” The wanted Clerics’ aide who described himself as Ali told reporters in Addis Ababa.

Asked about the sort of agreement reached with the ruling minority junta which led to the opening of the high way Ali replied by saying that he will only divulge the detail after Wednesday 20 March 2012 follow up discussion between the TPLF warlords and Afar elders in the town of Semera.

In addition Ali denied rumors that the beloved cleric had already fled to Saudi Arabia via Eritrea and assured all concerned that he is in Semera fulfilling his duties both as leader and religious elder.

“He will never leave his people and his people will never allow TPLF forces to go in and arrest an innocent man at gun point. What is his crime?”
infohorntimes@gmail.com
Source http://ecadforum.com/News/hands-off-our-leader-afar-warriors-warned-ethiopia/