Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Saturday, December 19, 2015

ሱሉልታ የደረሰው ሕዝባዊ ተቃውሞ አራት ኪሎ ይደርሳል በሚል ፍራቻ በሰሜን አዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ

 
sululta
(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ ክልል የተነሳውና የተቀጣጠለው የሕዝብ ቁጣ ሱሉልታ መድረሱን ዘ-ሐበሻ ቀደም ብላ መዘገቧ አይዘነጋም:: ሕወሓት የሚመራው መንግስት ሂሊኮፕተር ጭምር በማንቀሳቀስ ሱሉልታን ሲያምስ የዋለ ሲሆን ሕዝቡም የጎጃም መንገድን ዘግቶ እንደነበር ይታወሳል::
የሱሉልታው ሕዝባዊ ቁጣ አዲሱ ገበያ ከዛም አልፎ አራት ኪሎ ቤተመንግስት ይደርሳል ብሎ የሰጋው መንግስት ዛሬ በአዲስ አበባ ሰሜናማው ክፍል የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን ዘግቷል:: በተለይ ቀኑ አርብ በመሆኑና ቅዳሜና እሁድም በአዲስ አበባ ትምህርት ስለማይኖር እፎይታን አገኛለሁ ብሎ ያዳመረው መንግስት በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል ተብሏል::
እንደ ዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች ከሆነ ከሱሉልታ ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ የመኪና ጉዞዎች ከተቋረጡ 2 ቀናቸውን የያዙ ሲሆን በመንግስት ላይ ከፍተኛ የሆነ ጫናን ፈጥሮበታል:: ከአዲስ አበባ በሱሉልታ በኩል የሚያልፉ መንገዶችም ከተዘጉ እንዲሁ 2ኛ ቀናቸውን አስቆጥረው ሶሰስተኛቸውን ይዘዋል::
በአዲስ አበባ በማንኛውም ጊዜ ሕዝባዊ ቁጣው ይነሳል ተብሎ እየተጠበ ነው:: Source from http://www.zehabesha.com/amharic/archives/49233