Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Friday, December 20, 2013

የደቡብ ሱዳን የሥልጣን ሽኩቻ መዘዝ፣

የሰሜን ሱዳን የፖለቲካ ተጽእኖና ፤ የዐረብ ባህል ጫና አንገሽግሾት 22 ዓመታት መሪር ትግል ያካሄደው የደቡብ ሱዳን ህዝብ፤ ነጻነት ባወጀ በ 2 ዓመት ከመንፈቅ ገደማ ወደ አስከፊ የእርስ በርስ ውጊያ እንዳያመራ አሥግቷል። ባለፈው እሁድ በመዲናይቱ
በጁባ ያገረሸው ውጊያ ፣ የ 500 ያህል ሰዎችን ሕይወት ቀጥፎ ፤ 34,000 ሰዎች፤ በተባበሩት መንግሥታት ጣቢያዎች መጠለያ እንዲሻ አስገድዷል ። የሥልጣን መቀናቀን ነው የተባለለት ውዝግብ ፣ በጎሣ ልዩነት ተካሮ ባፋጣኝ ወደሌሎች አካባቢዎች መዛመቱ የሚታወስ ነው። ጉዳዩ ያሳሰባቸው የምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት ሚንስትሮች ፤ የአፍሪቃ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ተወካዮች ጁባ ውስጥ ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልባ ኪር ጋር በዛሬው ዕለት እንደሚወያዩ ይጠበቃል። ስለደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ይዞታ ፣ በፀጥታ ጉዳይ ተቋም፤ (ISS)የምሥራቅ አፍሪቃ ፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ በማነጋገር የተጠናቀረው ዘገባ የሚከተለው ነው።
ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ባለፈው ዓመት በሐምሌ ወር ምክትላቸውን ሪኤክ ማቻርን ከስልጣን ካሰናበቱ ወዲህ ቁርሾው አይሎ፣ የሥልጣን ሽኩቻው ባለፈው እሁድ መፈንዳቱ የሚታወስ ነው። የጎሣ ልዩነትን ብቻ መሠረት ባደረገ በዚያ የተኩስ ልውውጥም ሆነ የኃይል እርምጃ፤ ብዙ ሰዎች ያላበሳቸው የጥይት ራት የሆኑበት ድርጊት የተባበሩትን መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ኀላፊ ናቪ ፒላይን እጅግ እንዳሳዘነ ተመልክቷል። ራሳቸው የተ መ ድ ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን፤ በበኩላቸው ፣ ውዝግቡ ባስቸኳይ በፖለቲካ ውይይት መላ እንዲፈለግለት ነው ያስገነዘቡት።
አንዳንድ የ ምሥራቅ አፍሪቃ በይነ መንግሥታት (IGAD) አባል ሃገራት ውዝግቡን በቀላል ሊፈታ እንደሚችል በተስፋ ይሁን ዲፕሎማሲያዊ ፈሊጥ አድርገው ያን ያህል የሚያሳስብ እንዳልሆን መግለጫ ቢሰጡም፤ ተጨባጩ ይዞታ የሚያረጋጋ ሆኖ አልተገኘም። አንዳንድ መንግሥታት ዜጎቻቸውን ለማስወጣት አኤሮፕላኖች ን በመላክ ላይ ናቸው። አሶኬ ሙከርጂ የተባሉት ህንዳዊ የተባበሩት መንግሥታት ልዑክ፤ 3 ህንዳውያን ሰላም አስከባሪዎች፤ ሆን ተብሎ የጥይት ዓላማዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ዩጋንዳ ዜጎቼን ለመጠበቅ ነው በሚል ሰበብና ከጁባ መንግሥትም ጥሪ ቀርቦልኝ ነው በማለት ፤ በዛሬው ዕለት በደቡብ ሱዳን መዲና ጦር ሠራዊት አሠማርታለች። ትናንት ብርቱ ማስጠንቀቂያ ያሰሙት የዩናይትድ እስቴትሱ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ 45 ወታደሮቻቸው እንዲሠማሩ አድርገዋል። የዚህ ያልተጠበቀ መስሎ የቆየው ውዝግብ ፍንዳታ ዋና መንስዔው ምን ይሆን? ዋና ጽ/ቤቱ በፕሪቶሪያ ፤ ደቡብ አፍሪቃ በሚገኘው የፀጥታ ጉዳይ ተቋም ፣ የምሥራቅ አፍሪቃ የፖለቲካ ጉዳዮች ተንታኝ አንድርውስ አታ አሳሞዋ--
\ «ጉዳዩን ሰፋ አድርገን ካየነው፣ በፕሬዚዳንቱ ክብር ዘብ የተፈጠረ ምሥቅልቅል፤ የአገሪቱን የፖለቲካ ክፍፍል አሥፍቶታል። የጎሣ ልዩነትም እንዲጎን ነው ያደረገው። ቀስ በቀስምየጎሳ ልዩነትን በማባባስ፣ በፖለቲካው አመራር ለረጅም ጊዜ የቆየውን ክፍፍል በጦር ሠራዊቱና በብሔረሰቦችም ዘንድ ጥርጣሬውን ያባብሰዋል። ይህ ደግሞ፣ አገሪቱ ነጻነት ከማወጇ በፊት አንስቶ ብዙዎች ሲፈሩት የነበረውን ውዝግብ እውን ሊያደርገው በቅቷል።»

ደቡብ ሱዳን እ ጎ አ ከ 1983-2005 ባካሄደችው የ 22 ዓመታት መሪር የትጥቅ ትግል ከ 2 ሚሊዮን በላይ ተወላጆቿን እንዳጣች ነው ታሪኳ የሚያስረዳው። ስለሆነም ሰፊ መስዋእትነት የከፈለ ህዝብ አሁን እርስ በርስ እንዳይፋጅ ያሠጋበት አደጋ ስለመኖሩ በሚነገርበት ወቅት ውዝግቡ በቀላል እንደሚፈታ መገመት ይቻላል?
«ሳልቫ ኪርንና ሪኤክ ማቻርን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ማምጣቱ ከሞላ ጎደል ቀላል ሊሆን ይችላል። ይህ ግን ሁለቱን የፖለቲካ መሪዎች ወይም ተቀናቃኞች የሚመለከት ነው። ግን ፤ ጉዳዩ የዲንካና የኑኤር መቀናቀን መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም። በፖለቲካው መስክ በከፍተኛ አመራር ላይ ባሉት ቅራኔውን እንደምንም ማርገብ ቢቻል እንኳ በሀገሪቱ በመላ ሲብላላ የቆየው ችግር እንደምናስበው በቀላሉ ሊወገድ የሚችል አይደለም።»
የደቡብ ሱዳንን ውዝግብ፣ የካርቱምን መንግሥት በጥሞና ነው የሚመለከተው። በአንድ በኩል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ጋር የሚወያዩባቸው አንዳንድ ዐበይት የጋራ ጉዳዮች በአንጥልጥል እንዲቀሩ አይሻም። በሌላ በኩል የካርቱም መንግሥት ለአፈንጋጩ ሪኤክ ማቻር ሊያደላም ሆነ ሊደግፍ እንደሚችል የሚናገሩ አሉ። በደቡብ ሱዳን የተፈጠረው ውዝግብ እንዲወገድ ተጽእኖ በማድረግም ሆነ በመሸምገል መፍትኄ ሊያፈላልጉ የሚችሉ አገሮች ን መጥቀስ ያቻላል?

«የአካባቢው አገሮች፤ ዩጋናዳ ኬንያና ኢትዮጵያ ጁባን በሰፊው ማግባባት የሚችሉ ናቸው። ጎረቤቶች ስለሆኑ ብጻቻ አይደለም። ሰሙኑን ሳያገልሉ፣ በጦርነቱ ወቅት የተጫውቱት ሚና እጅግ ከፍ ያለ ነው። ደቡብ ሱዳን ለአነዚህ አገሮች ዐቢይ ከበሬታ ነው ያላት። ብዙዎች ደቡብ ሱዳናውያን፤ ኬንያን በአስተናጋጅነቷ ብቻ ሳይሆን ፤ ብዙ የሚያቀራርቧቸው ጉዳዮች እንዳሉም ይሰማቸዋል። ያም ሆነ ይህ «ኢጋድ» በመሪነት መላ ቢሻ በጣም ጥሩ ነው፤ ይሁንና ዩጋንዳን የመሳሰሉ አገሮችም ለደቡብ ሱዳን መልሶ ሰላም ለማስገኘት በከፍተኛ ደረጃ ተሰሚነት ያላቸው መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም።»
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሠ
To lessen from DW- Amharic Radio Click Here

Friday, December 6, 2013

The Worlds Icon Pass Away - Nilson R. Mandela

Nelson Rolihlahla Mandela (Xhosa pronunciation: [xoˈliːɬaɬa manˈdeːla]; 18 July 1918 – 5 December 2013) was a South African anti-apartheid revolutionary as well as a politician and philanthropist who served as President of South Africa from 1994 to 1999. He was the first black South African to hold the office, and the first elected in a fully representative election. His government focused on dismantling the legacy of apartheid through tackling institutionalised racism, poverty and inequality, and fostering racial reconciliation. Politically an African nationalist and democratic socialist, he served as the President of the African National Congress (ANC) from 1991 to 1997. Internationally, Mandela was the Secretary General of the Non-Aligned Movement from 1998 to 1999.

 http://upload.wikimedia.org/wikipedia/en/1/14/Nelson_Mandela-2008_%28edit%29.jpg
              Nelson Rolihlahla Mandela
 A Xhosa born to the Thembu royal family, Mandela attended the Fort Hare University and the University of Witwatersrand, where he studied law. Living in Johannesburg, he became involved in anti-colonial politics, joining the ANC and becoming a founding member of its Youth League. After the South African National Party came to power in 1948, he rose to prominence in the ANC's 1952 Defiance Campaign, was appointed superintendent of the organisation's Transvaal chapter and presided over the 1955 Congress of the People. Working as a lawyer, he was repeatedly arrested for seditious activities and, with the ANC leadership, was unsuccessfully prosecuted in the Treason Trial from 1956 to 1961. Although initially committed to non-violent protest, he co-founded the militant Umkhonto we Sizwe (MK) in 1961 in association with the South African Communist Party, leading a sabotage campaign against the apartheid government. In 1962 he was arrested, convicted of conspiracy to overthrow the government, and sentenced to life imprisonment in the Rivonia Trial.

Mandela served 27 years in prison, initially on Robben Island, and later in Pollsmoor Prison and Victor Verster Prison. An international campaign lobbied for his release, which was granted in 1990 amid escalating civil strife. Mandela published his autobiography and opened negotiations with President F.W. de Klerk to abolish apartheid and establish multiracial elections in 1994, in which he led the ANC to victory. As South Africa's first black president Mandela formed a Government of National Unity in an attempt to defuse racial tension. He also promulgated a new constitution and created the Truth and Reconciliation Commission to investigate past human rights abuses. Continuing the former government's liberal economic policy, his administration introduced measures to encourage land reform, combat poverty, and expand healthcare services. Internationally, he acted as mediator between Libya and the United Kingdom in the Pan Am Flight 103 bombing trial, and oversaw military intervention in Lesotho. He declined to run for a second term, and was succeeded by his deputy, Thabo Mbeki. Mandela subsequently became an elder statesman, focusing on charitable work in combating poverty and HIV/AIDS through the Nelson Mandela Foundation.
Although Mandela was a controversial figure for much of his life, he became widely popular following his release. Although right-wing critics who continued to denounce him as a communist sympathiser and terrorist, he gained international acclaim for his activism, having received more than 250 honours, including the 1993 Nobel Peace Prize, the US Presidential Medal of Freedom, and the Soviet Order of Lenin. He is held in deep respect within South Africa, where he is often referred to by his Xhosa clan name, Madiba, or as Tata ("Father"); he is often described as "the father of the nation".

Source : - From Wikipedia, the free encyclopedia.
May god bless his soul rest in peace as he give the world peace!

Sunday, December 1, 2013

በሳዉዲ የኢትዮጵያዉያን ችግርና መፍትሄዉ

ኢትዮጵያ በሳውዲ ካለ ይኖሩ የነበሩ ከ50,000 የሚበልጡ ዜጎችዋን ወደ ሀገራቸው መመለስዋን በያዝነዉ ሳምንት መጀመርያ ማስታወቁ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ችግር ያጋጠማቸውን ዜጎቹን የመመለሱን ተግባር ሲጀምር ቁጥራቸው 10,000 ይሆናል ብሎ ገምቶ ነበር።
ይሁንና፣ አሁንም በሳዉዲ ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸዉ ኢትዮጵያዉያን ቁጥራቸው በውል እንደማይታወቅ እና፤ ምናልባትም ቁጥሩ ከፍ ሊል እንደሚችል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በዚሁ በያዝነዉ ሳምንት ለዶይቸ ቬለ መግለፃቸዉ ይታወሳል። በሳዉዲ አረብያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በፀጥታ ኃይላት ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸዉ እና አሁንም በዚሁ ችግር ዉስጥ ያሉ ዜጎች ጥቂት እንዳልሆኑም እየተነገረ ነዉ። የዕለቱ የእንወያይ ዝግጅት በሳዉዲ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያንን ላይ ስለደረሰዉ ችግር አጠቃላይ ገጽታ እና በወቅቱ ዜጎችን ለመርዳት እየተደረገ ስላለዉ እንቅስቃሴ ባልደረባዪ ጀፈር አሊ፤ ተወያዩችን ይዞ ሐሳብ አሰባስቦአል።
ጀፈር አሊ
አዜብ ታደሰ

Audios and videos on the topic