Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Sunday, June 30, 2013

የፕሬዚደንት ኦባማ የደቡብ አፍሪቃ ጉብኝት

አፍሪቃ

የፕሬዚደንት ኦባማ የደቡብ አፍሪቃ ጉብኝት

በሴኔጋል የሁለት ቀናት ይፋ ጉብኝት ያጠናቀቁት የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ትናንት ምሽት ደቡብ አፍሪቃ ገብተዋል። ይሁንና፣ የቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ኔልሰን ማንዴላ በጠና የታመሙበት ሁኔታ በፕሬዚደንት ኦባማ ጉብኝት ላይ ጥላ አጥሎበታል።
ምንም እንኳን የደቡብ አፍሪቃ ፖለቲከኞች የሀገራቸው እና የዩኤስ አሜሪካ የጋራ ግንኙነትን ለማጉላት ቢሞክሩም፣ ደቡብ አፍሪቃውያን በወቅቱ የሚያሳስባቸው የብሔራዊው ውድ እና ጀግና ኔልሰን ማንዴላ ጤንነት ብቻ ነው።
« የማንዴላ ምግባር ፣ ቆራጥ ሰዎች፣ በጎ ፈቃድ ያላቸው እና ለትልቅ ዓላማ የተነሱ ሰዎች ባንድነት በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ፣ በዓለም ምን ሊሰራ እንደሚችል በግልጽ አሳይቶኛል። በእርግጥ በዚህ ቅፅበት ሀሳባችና እና ፀሎታችን ከደቡብ አፍሪቃ ሕዝብ እና በተለይም ከማንዴላ ቤተሰቦች ጋ ነው። »
ፕሬዚደንት ኦባማ በሴኔጋል ጉብኝታቸው ወቅት የቀድሞውን የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ኔልሰን ማንዴላን « የዓለም ጀግና» በሚል ሲያሞግሱዋቸው፣ ባልተቤታቸው ምሸል ኦባማ ደግሞ በመዲናይቱ ዳካር አንድ ትምህርት ቤት በጎበኙበት ጊዜ ተማሪዎቹ ራሳቸው አንድ ቀን አኩሪ ታሪክ ተተው ማለፍ እንዲችሉ የማንዴላን ምግባር ሁሌ እንዲያስታውሱ ጥሪ አሰምተዋል።
ያም ሆነ ይህ ግን የፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ በአፍሪቃ ጠንካራ የኤኮኖሚ ኃያል መንግሥት ደቡብ አፍሪቃ የሚያካሂዱት ብዙ የተጠበቀው ጉብኝታቸው ያን ያህል የሕዝቡን ትኩረት ሳያገኝ ሊያልፍ የሚችልበት ስጋት ተደቅኖበታል። በተለያ ግዙፉ የፀጥታ ጥበቃ ጉዳይ ደቡብ አፍሪቃውያንን ብዙ እያነጋገረ ነው። በተለይ የዩኤስ አሜሪካ ጦር ብላክ ሆክ ሄሊኮፕተር በጆሀንስበረገ ከተማ ዝቅ ብሎ ሲበር ከታየ በኋላ አንድ ደቡብ አፍሪቃዊ አሜሪካውያን ሀገሪቱን ሊቆጣጠሩ ነው እንዴ ሲል በትዊተር አጠያይቋል። « ዘ ስታር» የተሰኘው የሀገሪቱ ጋዜጣ ደግሞ ከኦባማ ይበልጥ ጆርጅ ዳብልዩ ቡሽ በአፍሪቃ የሚታይ ነገር ሰርተዋል ሲል ጽፏል።
ይሁን እንጂ፣ የኦባማ ጉብኝት ግዙፍ የስራ አጥነት ችግር ለተደቀነባት ዴሞክራሲያዊቱ ደቡብ አፍሪቃ ከፍተኛ ትርጓሜ መያዙን የሀገሪቱ ፕሬዚደንት ጀኮብ ዙማ ብቻ ሳይሆኑ ሚንስትሮቻቸው ሳይቀሩ ተናግረዋል። ከዋነኞቹ የደቡብ አፍሪቃ የንግድ ሸሪኮች መካከል ዩኤስ አሜሪካ አንዷ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪቃ የሚገኙት 600 አዩኤስ አሜሪካ ተቋማት በሀ,ገሪቱ 120,000 የስራ ቦታ ፈጥረዋል። ዩኤስ በ 2010 ዓም በደቡብ አፍሪቃ ያንቀሳቀሰችው ቀጥተኛ ወረት 6,5 ቢልዮን ዶላር ነበር።

የቀድሞው የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ቢል ክሊንተን ለአፍሪቃ ባስተዋወቁት አጎዋ በተባለው ልዩ የንግድ ስምምነት መሠረት ደቡብ አፍሪቃ ወደ ዩኤስ አሜሪካ በንግድ ከምትልከው ዕቃና ምርት፣ በተለይ ጨርቃ ጨርቅ መካከል፣ 90% በቅናሽ ወይም ካለቀረጥ ይገባል። ደቡብ አፍሪቃ እና ዩኤስ አሜሪካ ለደቡብ አፍሪቃ ተጨማሪ የተመቻቸ የንግድ ሁኔታ የሚፈጥረውን በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ ቲፋ በመባል የሚታወቀውን የንግድ እና የኢንቬስትመንት ማዕቀፍ ስምምነት በ 2012 ዓም ተፈራርመዋል። ሚለር ማቶላ በውጭ ንግድ ላይ የተሰማራ « ብራንድ ሳውዝ አፍሪካ» የተባለው ተቋም ዋና ስራ አስኪያጅ ናቸው።
« የኦባማ የደቡብ አፍሪቃ ጉብኝት የሀገራችንን የኤኮኖሚ የወደፊት ዕድል እንዲያሻሽል ንእና ተጨማሪ ካፒታል ወደ ደቡብ አፍሪቃ እንዲመጣም እንፈልጋለን። በአሁኑ ጊዜ ዩኤስ አሜሪካ ዕቃ በንግድ ወደ ውጭ የምንልክባት ሁለተኛዋ ትልቋ ገበያችን ስትሆን፣ ወደ ሀገር በንግድ የምናስገባውን ዕቃ የምገዛባት በሦስተኛ ደረጃ የምትገኝ ሀገር ናት። ይህን ማሳደግ እንችላለን ብለን እናምናለን። እና ንግድን በተመለከተ ጉብኝቱ ለኛ ለደቡብ አፍሪቃውያን ብዙ ጥቅም ያስገኛል ብለን ተስፋ አድርገናል። »
ግን ሁሉ ደቡብ አፍሪቃውያን አይደሉም አሜሪካዊውን እንግዳ እጃቸውን ዘርግተው የሚቀበሉት። የሙሥሊም ጠበቆች ህብረት፣ በምሕፃሩ ለምሳሌ በሣምንቱ አጋማሽ በኦባማ ላይ በስብዕና አንፃር ወነጀል ፈፅመዋል በሚል የእስር ማዘዣ ለማውጣት ሞክሮ ነበር። ሙከራው ውድቅ ሆኖዋል። ህብረቱ ኤም ኤል ኤ ኦባማን በፓኪስታን እና በሶርያ ለ3000 ሰዎች ሞት ወይም መቁሰል ተጠያቂ አድርጓል። ይሁን እንጂ፣ ኤም ኤል ኤ በማህበራዊው የመገናኛ ዘርፍ ብዙ ወቀሳ ተፈራርቆበታል። የጆሀንስበርግ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና መምህራን ለፕሬዚደንት ኦባማ የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ለመስጠት በተያዘው ዕቅድ ላይ በወቅቱ ጠንካራ ክርክር ይዘዋል። አክራሪ ተማሪዎች ዕቅዱን በጥብቅ ተቃውመውታል።
የመገናኛ ብዙኃን ስለኦባማ ጉብኝት መነጋገር በያዙበት በዚሁ ጊዜ ግን በሰው ቤት ተቀጥራ የምትሰራው ፕሪቲ ናይሌያ ሀሳቧ በጠና ከታመሙት ማንዴላ ጋ ነው።
« በአሁኑ ጊዜ ትኩረታችን ያረፈው በማንዴላ ላይ ነው። ኦባማን ለማስተናገድ ጥቂት ጊዜ ብቻ ነው ያለን። ሀሳባችን ከማንዴላ ጋ ነው። ከዚህ በተረፈ ደግሞ ለአፍሪቃ ያን ያህል ፍላጎት ያላቸው አይመስለኝም። እርግጥ፣ ላንዳንድ አፍሪቃውያት ሀገራት ትኩረት ሰጥተዋል፣ ግን ሁሉም አይደሉም ከዚሁ ጥቅም የሚያገኙት። »
ሉድገር ሻዶምስኪ/አርያምተክሌ
መሥፍን መኮንን

Audios and videos on the topic

Sunday, June 23, 2013

Obang Metho’s Testimony before the Subcommittee on Africa

June 20, 2013

Testimony before the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations. Given by: Mr. Obang O. Metho, Executive Director Solidarity Movement for a New Ethiopia

“Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights”

I would like to thank the Chairman of the Committee on Foreign Affairs, Congressman Edward Royce, and all ranking members of the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations for this important opportunity to examine the Ethiopian Government’s observance of democratic and human rights principles in post-Meles Ethiopia.

I want to especially thank Congressman Christopher Smith, the Chairman of the Subcommittee on Africa for his extraordinary leadership in bringing the case of Ethiopia to the attention of this subcommittee once again; particularly in light of the many pressing global issues. In 2006, Congressman Smith worked hard to bring this issue all the way from subcommittee to the House, where it faced obstacles and died. I hope this time, something more concrete and productive can be accomplished for the betterment of both our countries.

In 2006, I gave testimony at that previous hearing in regards to the massacre of 424 members of my own ethnic group, the Anuak, in 2003, perpetrated by members of the Ethiopian National Defense Forces. I also testified regarding the ongoing crimes against humanity and destruction of property and infrastructure in the Gambella region of Ethiopia; however, because similar abuses were being perpetrated in other places in the country, I also spoke of the 193 peaceful protestors who were shot and killed as they peacefully protested the results of the flawed 2005 national election and the repression in Oromia. This also included testimony regarding the imprisonment of opposition leaders, including Dr. Berhana Nega, who is sitting next to me today. Please to read more open the link http://ecadforum.com/2013/06/20/obang-methos-testimony-before-the-subcommittee-on-africa/

Monday, June 17, 2013

የኢትዮጵያን ደስታ የፊፋ ዜና አቀዘቀዘው

 by Fisseha Tegegn
አዲስ አበባ ላይ የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድንን ያስተናገደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጌታሁን ከበደ እና የደቡብ አፍሪካው የፊታ አጥቂ በርናርድ ፓርከር በራሱ ጎል ላይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች 2 ለ 1 አሸንፏል…
የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን በተላይ በመጀመሪያዎቹ 20 እና 25 ደቂቃዎች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የመሀል ክፍል ኳሱን እንዳይቆጣጠር ለማድረግ በሚል ተጭኖ የተጫወተ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ሰባት እና ስምንት የደቡብ አፍሪካ ተጨዋቾችን የኢትዮጵያ ቡድን ግማሽ ሜዳ ላይ ማየት የተለመደ ነበር።

ባፋናን የረታው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን
ሆኖም የጨዋታውን የመጀመሪያ የጎል ማግባት እድል የፈጠረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሲሆን ሳልሀዲን ሰኢድ በግንባሩ የገጨውን ኳስ የደቡብ አፍሪካው ግብ ጠባቂ ኩኔ አድኖበታል።
15ኛው ደቂቃ ላይ ሳልሀዲን ሰኢድ ከርቀት በግሩም ሁኔታ የሞከረውን ኩኔ እንደገና ጎል ከመሆን ሲያከሽፍበት፣ ብዙም ሳይቆይ ፓርከር ከሌሾሎንያኔ የተቀበለውን ኳስ መትቶ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ጀማል ጣሰው በግሩም ሁኔታ አድኖበታል።

ጨዋታው ግማሽ ሰአት ያህል እንደተጓዘ ፋላ ከማእዘን ምት ያሻማውን ኳስ ማቶሆ በጭንቅላቱ በመግጨት የሞከረውን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ጀማል ጣሰው በቡጢ የመለሰው ኳስ ፓርከር ጋር ደርሶ ለደቡብ አፍሪካው ካይዘርስ ቺፍስ ክለብ የሚጫወተው የፊት አጥቂ ያደረገውን የጎል ሙከራ የግቡ መስመሩ ላይ ቆሞ ሲጠብቅ የነበረው አይናለም ሀይሉ በአስደናቂ መከላከል ጎል ከመሆን አድኖታል።
የጨዋታው የመጀምሪያ ጎል የተገኘው 34ኛው ደቂቃ ላይ ሲሆን በረኛው ኩኔ በረጅሙ ወደ ኢትዮጵያ ሜዳ የመታውን ፓርከር ከኢትዮጵያ ተከላካዮች ፈጥኖ በመሮጥ የመታው ኳስ ጀማል ጣሰውን አልፋ መረብ ላይ በማረፏ ደቡብ አፍሪካ ጨዋታውን 1 ለ 0 እንድትመራ አስችሏታል።

የደቡብ አፍሪካ መሪነት የቆየው ግን ስምንት ደቂቃ ያህል ብቻ ሲሆን የመጀመሪያው ግማሽ የጨዋታ ክፍለ-ጊዜ ሊጠናቀቅ ሁለት ደቂቃዎች ያህል ሲቀሩት አዲስ ህንጻ፣ ሽመልስ በቀለ እና ጌታነህ ከበደ ያደረጉት ቅብብል የፈጠረውን የጎል ማግባት እድል ጌታነህ ከበደ በግሩም ሁኔታ ከመረብ አሳርፎ የመጀመሪያው ግማሽ የጨዋታ ክፍለ-ጊዜ 1-1 ተጠናቋል።

በሁለተኛው ግማሽ የጨዋታ ክፍለ-ጊዜም ልክ እንደ መጀመሪያው ሁሉ ደቡብ አፍሪካ ተጭኖ የተጫወተ ቢሆንም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጠንካራ የመከላከል እንቅስቃሴ ጥቃቱን ለመቋቋም አልተቸገረም ነበር። በተለይ ተቀይሮ የገባው ራንቴ ሜዳ ከገባ ብዙም ሳይቆይ ሁለት አደገኛ የጎል ማግባት ሙከራዎችን ቢያደርግም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የመከላከል እንቅስቃሴሴ እና የራሱም የአጨራረስ ድክመት ሙከራውን አክሽፎበታል።
70ኛው ደቂቃ ላይ አበባው ቡጣቆ በቅጣት ምት ወደ ደቡብ አፍሪካ የፍጹም ቅጣት ምት ክልል የላከውን ኳስ የደቡብ አፍሪካው ፓርከር በግንባሩ ገጭቶ ባልተጠበቀ ሁኔታ በራሱ ጎል ላይ ግሩም ጎል በማሳረፉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሊመራ ችሏል።

የጨዋታው የመጨረሻ 15 ደቂቃዎች በአብዛኛው ደቡብ አፍሪካ ጎል ለማግባት በሚያደርገው ማጥቃት፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ደግሞ ውጤት አስጠብቆ ለመውጣት እና በሚገኙ አጋጣሚዎች ኳሱን ወደፊት ለሳልሀዲን ሰኢድ እና ጌታነህ ከበደ በመላክ በማጥቃቱ ላይ በመሳተፍ በሚያደርጓቸው ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንቅስቃሴዎች ከተጓዘ በኋላ በኢትዮጵያ 2 ለ 1 አሸናፉነት የተጠናቀቀው።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየት፦
“ይሄ ተአምር ነው። ዛሬ በምንም ቃል ሊገለጽ የማይችል ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ቀን ነው። ደቡብ አፍሪካ በመጀመሪያው ግማሽ ተጭኖን ተጫውቷል። ጠንካሮችም ነበሩ። በሁለተኛው ግማሽ ግን የአጨዋወት ለውጥ በማድረግ ሁለቱ የተመላላሽ ስፍራ ተጨዋቾችቼ አጥቅተው እንዲጫወቱ አደረኳቸው።
“ምክንያቱም በሜዳችን እንደመጫወታችን አቻ መውጣት በቂያችን አልነበረም። በደጋፊያችን ፊት ማሸነፍን እፈልግ ነበር። በርግጥ ያሸናፊነቷን ጎል የሰጠን ደቡብ አፍሪካዊ ተጨዋች ነው። ምን አልባት እግርዚአብሄር ድሉን ለኛ ሊሰጠን ስለወሰነ ይሆናል ያ የሆነው” ብለዋል።
የደቡብ አፍሪካው አሰልጣኝ ጎርደን ኢገንሰንድ ቡድናቸው ቢሸነፍም የተጋጣሚያቸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እና ደጋፊውን ከማድነቅ ወደኋላ አላሉም።
“ኢትዮጵያዊያንን እንኳን ደስ ያላችሁ እላለሁ። በጣም አስቸጋሪ ጨዋታ ነበር። በተላይ ደጋፊዎቻቸው ግሩም ነበሩ” ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከዚህ ውጤት በኋላ ምድቡን አንድን በ13 ነጥብ በመምራት አንድ የምድብ ጨዋታ እየቀረ በጥሎማለፍ መልክ ወደሚካሄደው የቀጣዪ ዙር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ማለፏን ቢያረጋግጥም የአለም አቀፉ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፊፋ እሁድ ማምሻውን ባወጣው ዜና “የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአለፈው ሳምንት ቦትስዋናን 2 ለ 1 በረታበት ጨዋታ ላይ ተሰልፎ መጫወት ያልነበረበት ተጨዋች አሰልፎ አጫውቷል” በሚል ምርመራ እንደሚደረግበት ማስታወቁ በኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈጠረውን ታላቅ የደስታ ስሜት አደብዝዞታል።
ፊፋ ኢትዮጵያን ጨምሮ በቶጎ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ላይ ተመሳሳይ ምርመራ የከፈተው የፊፋ የውድድር እና ስነ-ስርአት መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 55 እና የብራዚሉ አለም ዋንጫ ማጣሪያ መተዳደሪያ ደንብ ላይ አንቀጽ ስምንትን በመጥቀስ ነው።
የፊፋ የውድድር እና ስነ-ስርአት መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 55
የፊፋ የውድድር እና ስነ-ስርአት መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 55
የፊፋ የጨዋታ መዝገቦች እንደሚያሳዩት ከሆነ ምን አልባት መጫወት ሳይኖርበት የተጫወተው ምንያህል ተሾመ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር 1 ለ 1 በተለያየችበት እና አዲስ አበባ ላይ ቦትስዋናን 1 ለ 0 በረታችበት ጨዋታዎች ላይ የቢጫ ማስጠንቀቂያ ካርዶች ያየ በመሆኑ በአለፈው ሳምንት ኢትዮጵያ ወደ ሎባትሴ አቅንታ ቦትስዋናን 2 ለ 1 በረታችበት ጨዋታ መሰለፍ አልነበረበትም።

Friday, June 14, 2013

Egypt's Limited Military Options to Stop an Ethiopian Dam Project

Egypt's Limited Military Options to Stop an Ethiopian Dam Project
The Blue Nile in Guba, Ethiopia, during its diversion ceremony on May 28. (William Lloyd-George/AFP/Getty Images)

 

 

 

                                        The Blue Nile in Guba, Ethiopia, during its diversion ceremony on May 28. (William Lloyd-George/AFP/Getty Images)

Summary

Ethiopia's initiation of a dam project on the Blue Nile has quickly drawn the ire of Egypt, which is critically dependent on it as a source of much of the country's freshwater needs. As Egyptian Foreign Minister Mohamed Kamel Amr said June 9 following Ethiopia's refusal to halt construction of the dam and ahead of his trip to Addis Ababa to discuss the project, Egypt will not give up a "single drop of water from the Nile." "No Nile, no Egypt," he said.

While Egypt has struggled to attract diplomatic intervention on its behalf to thwart Ethiopia's dam construction, tensions have reached the point where Egypt has suggested the use of force to keep the dam from potentially lowering the Nile's water levels downstream to unacceptable levels. There will be serious international pressure to keep the dispute over the dam in the realm of diplomacy, but there are also fairly significant constraints on the physical possibility of an Egyptian military solution.
To read more about pleas open the link Nile Dame

Saturday, June 8, 2013

Congratulation! Menbere.

 Great woman I thank you and I am proud of you for being a good example and contribute ur share as Ethiopian and as a good successful citizen! "If you went it you can find a way" 

2013 Commencement Address - Menbere Aklilu

Wednesday, June 5, 2013

ከሞላ ጎደል የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍን ትክክለኛ ገጽታ የሚያሳይ ቪዲዮ


ኢ.ቲ.ቪ ከበሩ ላይ እንኳን የሚፈፀምን ተግባር ቀጥታ እንደወረደ የማስተላለፍ ችሎታ የለዉም እንዴ ወዳጆቸ?? ምን አይነት የቴክኒክ ችግር አጋጥሟቸዉ ይሆን ይችን እንኳ በመቅረፀ ድምፅ መመዝገብ ያቃታቸዉ ?? ማን ይሆን ይህን ዘላለማዊ የሃሰት ቫይረስ የለቀቀባቸዉ?? አሁንስ የ ፎቶ ሾፒንግ እና የ ቪዲዮ ኢድቲነግን ፈጠራወች ጠላኋቸዉ፡፡ ለነገሩ ኢ.ቲ.ቪ. እንድህ ለሰይጣናዊ ተጋባር ይጠቀማቸዋል ብለዉ አላሰቡም ነበር የሚባል ሃሜት አለ፡፡

(ሊያዩት የሚገባ)ከሞላ ጎደል የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍን ትክክለኛ ገጽታ የሚያሳይ ቪዲዮ
(ምንም የመብት ጥያቄ በቁጥር መወሰን ባይኖርበትም) የመንግስት ባለስልጣናትና ደጋፊዎቻቸው የቁጥር ጨዋታ ውስጥ በመግባት ሊያሳንሱትና ሊቀንሱት የፈለጉትን ሰልፈኛ እንደ ረጋ ውሀ ተከማችቶ ይመልከቱት፦

https://www.facebook.com/photo.php?v=514670045254096

 

NOT EVEN ONE DAY PASS WHEN TPLF ACCUSED THE BLUE PARTY LEADERS !

Monday, 3 June 2013

what is funny about TPLF's tactic is that after allowing the demonstration for their own propaganda of being called democratic , which they already know about the peaceful questions the protester has before  they even went and ok with it, then it is not even one night pass Tplf  start accusing  the blue party leaders for the questions they brought in the demonstration by claiming the questions are against the Law,how convenient is that? ,.

The government said that The blue party has brought Two questions that against the Law
  1. The question release of innocent prisoners which has been convicted with terrorist action,
  2. Ask the government to stop interference with a religious matters.




Tplf says that, the question of release of prisoners are not fair while  their case is still taken  in court  and the gov't has been accused interference of religion matters while the government hasn't done such a thing  ,how funny is this.


Minister of Government Communications Affairs Shimelis Kemal said also the question of to stop the eviction has been resolved and taken action by the government before the protester went out and it is already corrected .  while it is known the forceful eviction is still continues in different region of Ethiopia.

Finally ETV  the mouth of TPLF has been forced to speak some truth about the demonstration so that the Minister has to warn and
convict the Blue party leaders and the people so that  it will be very dangerous if it is going to continue after 3 months of time as the blue party leader says and if the people are  awaken and motivated to stand for its own rights .

Thanks to technology this days modern mobiles are available to take pictures and record videos to expose TPLF what ETV can not hide, is possible to send in MMS, FB, and in diffrent social Networks.

Source from http://voiceofree.blogspot.no/

Monday, June 3, 2013

Thousands march for rights in rare Ethiopia protest - Yahoo! News

Thousands march for rights in Ethiopia

More Pictures from http://www.flickr.com/photos/freeourleaders/8922447665/in/set-72157633873751499                        
http://news.yahoo.com/thousands-march-rights-rare-ethiopia-protest-160548831.html
By Aaron Maasho ADDIS ABABA (Reuters) - About 10,000 Ethiopians staged an anti-government procession on Sunday in the first large-scale protest since a disputed 2005 election ended in street violence that killed 200 people. The demonstrators marched through Addis Ababa's northern Arat Kilo and Piazza districts before gathering at Churchill Avenue in front of a looming obelisk with a giant red star perched on top, a relic of Ethiopia's violent Communist past. Some carried banners reading "Justice! Justice! Justice!" and some bore pictures of imprisoned opposition figures. ...
Read the full story