Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Saturday, November 17, 2012

እንዲህ ያለ ዘመን የተገላቢጦሽ

    
      የተገላቢጦሽ!
እንዲህ ያለ ዘመን የተገላቢጦሽ
አህያ ወደ ቤት ውሻ ወደ ግጦሽ!
የተባለው ብሂል በይፋ ላይ ዋለ
በወያኔ ዘመን ብህግ ተከለለ
መጻፍ መናገርን ወያን ከለከለ
ኣልፎ ተርፎም ደግሞ በስር ቤት ኣዋለ
የሚገልባብጥ መምሪያ ስላለ።

የሙስናዋ እናት እሷ አዜብ እያለች
ሀቢባ በሰበብ ወደ እስር ቤት ገባች።
እስኪ እናነጻጽር ሁለቱን አውገረድ
ማን እንደሚጠየቅ ህግ በመረማመድ
እረ የት እና የት ከምኑ እንጀምር
የፈጸሙት ጥፋት ሰማይ እና ምድር
እንዲህ ለናሙና ትንሽ እንናገር
ዘቢብ ስታቀብል አዜብ ስትቆልል
ጠዋት ማታ ሰለል
ኣልፎ ተርፎም መግደል
ከስልጣን ላይ ሆኖ ያለ ህዝብ ወኪል
ከነ ባሎቻቸው በህዝብን በመከለል
ነበረ ነገሱት እንዲሁ ያለ ውል።


                       የባል ባላደራ ኢፈርት ሊጠበቅ
                          የሜጋ ባለት ባለትልቅ ፎቅ 
                          የመሪ ነጋ ያውም ባለሱቅ
                      ዶላሩንንዛሪ የእስፔን ባለ ወርቅ
                      አዜብ ነዋይ ፍቅሯ ለመንዴላቀቅ
                      ከሌላም አይደለ ደሃን በመንጠቅ
                      እስኪ እናወዳድር -
                      ካማት ባላደራ መስጅድ ለመስደቅ
                      ለማሰራት ስትል ቃል ለመጠበቅ
                      ሃቢባ ለፅሎት ስውን ለማፅዴቅ
                      እርዳታ ፍለጋ እጅ በመናፈቅ
                      እናንተው ፍረዱ እንግዲህ በሀቅ
                      ከቶ ማን አጠፋ አሁን ለግረሙቅ።

21 አመት እንግሰው ባኖሩ
ኃልፊነት ወስደው ስላስተዳደሩ
ጁነድን በከንቱ እያሉ እሽሩሩ
መካካድ ልምዳቸው ተጣስ ደንበሩ
የማይረሙ ይዛፍ እንቅልፍ ክብሩ
ከስልጣን አውርደው በስር አስፈራሩ
ትልልቅ ዘርፊ ሞልቶ ያገር ቁሩ
የተገላቢጦሽ ሁኑዋለ ሚስጥሩ
በወያኔ አካሄድ ያውም ባመራሩ 
የዋሁን ሰው ሁሉ ከዘብጥያ ኣጎሩ።

                       በማማ ኢትዮጲያ በዛች ባለ ታሪክ
                       ያዜብና ግድፈት አያልቅም ቢተርክ
                       መለስን ተማምና ተመልክታ እንድምላክ
                       ፈጣሪ እና አንዋሪን ዘንግታው በምትክ
                       ከሷዋ ያልግጠመን ማዋከብ መነትረክ
                       ስራዐቱን አርጋው እከክልኝ ልከክ
                       ለሱዋ ያልተገዛን ቻርተር አላከበርክ
                       እያለች መበቀል ተነሳ ተንበርከክ
                      በቀጭን ትእዛዝ አጠፋች ከመድረክ

ቤተ መንግስቱንም ገራገረች አሉ
ጉድ አለ አለማችን ተገርሞ በሙሉ
ግራ ቢሆንበት አድርጎቱዋ ሁሉ
አይሰማው የለም ገዥ ቤት አጣ ኣሉ
ሲወጣ ሲጋባ ጨለማ ክልልሉ
የተገላቢጦሽ ደሳለኝ ተሿሚው ተንቀዋለሉ
ባለም ተነገ የመሪ ቤት አልባ ሁነዋል ተባሉ
አዜብ መች ህግ አውቃ ልቡዋ ነው ከልሉ።

  ደግሞ በሚድያ ሌላ ጉድ ነገሩን
                              የመለስ ራዓይ ለተግራይ ማድላቱን
                              ፕሮጀክት ፅፎዋል አሉ እና አሳወቁን
                               ሙዋች ባለ ራዓይ አሁንም አልተውን
                              ግባዓቱን ከድኃ ብግድ ሊነጥቁን
                              ዘመናዊ ሊያደርግ ነጥሎ ትውልድን
                              ሸቀጥ ከንዱስትሪ ለኛ ሊሸጡልን
                              ቃለ መጥይቁን አየን ተከታተልን                             
                             ምሰእዋት ለኢትዮጵያ ሁኑዋል እያሉን
                             በአፍ ወለምታም ቢሆን እውነቱን አወቅን
                             ብሄራዊ ስይሆን ጎጠዊ መሆኑን
                             እንዲነትን ትቶ ከፋፋይነቱን
                             እውነት እና ንጋት እያደር ጠራልን 
                             ይታዴግ ሚድያ ዘመንመጣልን
                             ከኑዛዜ እድርሿ ቃሉን አሳወቀን።
አጀብ አለ ያገር ሰው በግርምት ሲጉላላ
ምን ሰውን ብትንቅ ለዘር ብታደላ
ተተኪንም ገዥ ብትንቅ ብታጥላላ
ምን አለ በሚስጥር ብታይዝ ይህን ሁላ
ዘፈኑ እንኩዋን ነበር እንዳው መላ ገላ
ለሴት ልጅ ሲነገር እንድትፈልግ መላ
ወይስ ምን አባቱ ምን አለው ኬሌላ
ፖለቲካን እንደሁ ዘዋሪ እኛ ብላ
የተገላቢጦሽ እንዲሆን የምትፌልግ የጊዜ ቀምጣላ
እንዲህ ትሰር ትዝረፍ የልቡዋ እንዲሞላ
ተመቻችቶላታል እሱዋማ ምንትላ።

                        ግን! ታሳሪወች እና ተነጣቂም እኛ በዛብን በዴሉ
                        በቁማችን ጋጠን ወያኔ ተንኮሉ
                        እረ አይሆንም በቃ - እንቢ ባንድ በሉ
                        ያገር ሰው ተባባር አይጥፋብህ ውሉ
                        በየቦታው ያብብ ህዝባዊነት ትግሉ
                        ከትካሻህ ይወረድ ወያኔ እንዝላሉ
                        ብዙሃን ይወስን ይቅር መደለሉ
                        ይታረም ከንግዲህ የማይመስል ሁሉ
                        የተገላቢጦ ያለ አግባብ መዋሉ።

እንደዛ እንደ ጥንቱ እንደ የካቲቱ
ሙስሊም ክርስቲያኑ በአንድ ላይ ክተቱ
ወርቃማው ጊዜችን አይለፍ በከንቱ
በዛብን በዴሉ መታሰር መሞቱ
ቅርሶች እይውዴሙ ይከበር እምነቱ
የሄ መሰሪ ሃይል ይመታ ካናቱ
ስብአዊነት ይስፈን በቃን እንግልቱ
ሁሉም መስመር ይያዝ ይከበር ስሪቱ።

ተጻፈ በያቆብ ተክሌ አርጋው - ህዳር 1/2005
ለማግኘትargawya@gmail.com

No comments:

Post a Comment