Yakob's Point of Views and News, Ethiopian politics and News, Cultures, Musics etc

Tuesday, February 19, 2013

በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ፖለቲካዊና ማኀበራዊይዘት ያላቸው መፅሔቶችና መፅሐፎችእንዳይሸጡ ታገደ::

Tuesday, February 19, 2013

በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ፖለቲካዊና ማኀበራዊይዘት ያላቸው መፅሔቶችና መፅሐፎችእንዳይሸጡ ታገደ፤ አዙረው የሚሸጡወጣቶችም ከየካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮየያዙዋቸው እንደተወረሰባቸውም ታውቋል፡፡
በተለይ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 11 ልዩስሙ አባጃሌ በሚባል አካባቢ ያሉ የደንብአስከባሪዎች እዚህ ጎንደር ውስጥ ምንምዓይነት ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውንመፅሔቶች፣ ጋዜጦችና መፅሐፎችመሸጥ አትችሉም በሚል በተደጋጋሚጊዜ ከአዙአሪዎች እየወረሱ ቅጣት እያሉያስከፍሏቸው እንደነበር ቢታወቅምየካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ግን ሙሉበሙሉ እንደወረሱባቸው ተጠቁሟል፡፡
በአካባቢው ጋዜጣ፣ መፅሔትና መፅሐፍእያዞሩ ከሚሸጡት ወጣቶች መካከልአብዛኞቹ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችተመርቀው ስራ አጥ የሆኑ እንደሆነምምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
ወጣቶቹ የተወረሱባቸውን ንብረቶችለማስመለስ ወደ አካባቢው መስተዳደርስራ አስኪያጅ ቢያመሩም ሥራ አስኪያጁ“የተወረሰባቸው የወጣቶቹ ንብረትሊመለስ ይገባል ፣ ወንጀል እስካልፈፀሙድረስም አዙረው መሸጥ ይችላሉ” ቢሉምየደንብ አስከባሪዎቹ ለመመለስ ፈቃደኛአለመሆነቸውን ማስታወቃቸው ተጠቁሟል፡
፡ የደንብ አስከባሪዎችም የአካባቢውንየብአዴን/ኢህአዴግ የድርጅት ጉዳይኃላፊ የሆኑት አቶ አያና ካልፈቀዱ
ይመለስላቸውም ያሉ ሲሆን አቶ አያናምየተወረሱት መሔቶችና መፅሐፎችእንዲወረሱ ትዕዛዝ መስጠታቸው ታውቋል፡፡

ወጣቶቹም በሁኔታው እጅግ ከማዘናቸውበተጨማሪ “ጋዜጦች፣ መፅሔቶችናመፅሐፎቹ የሚታተሙት አዲስ አበባየመንግስት ኃላፊዎች በሚያውቁት ህጋዊመንገድ ሆኖ ሳለ ጎንደር እየመረጡ አትሽጡመባላችን ምክንያቱ አልገባንም፣ የጎንደርህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያ ህዝብ ተለይቶየሚታተሙ ህጋዊ ፅሑፎችን አታንብቡ፣መረጃም አታግኙ እንደማለት ይቆጠራል፤እኛንም ሰርታችሁ አትብሉ እንደማልት ነው”
ሲሉ ያላቸውን ቅሬታ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
በከተማው ያነጋገርናቸው እንዳንድአንባቢዎች በበኩላቸው “በተለይ በጎንደርየኢህአዴግ ባለሥልጣናት በሚፈፅሙትሙስና እና ብልሹ አሰራር በህዝቡ ላይ ከፍተኛጫና ፈጥሯል፡፡ ህዝቡ መረጃ እንዳያገኝማድረጋቸውም አዲስ አይደለም፤ ይህም ህዝቡላይ ከፍተኛ ቁጣን እየቀሰቀሰ መሆኑ ግልፅ
neው” ሲሉ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

ጉዳዩ የሚመለከታቸው የአካባቢው የፀጥታዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ አዶዬ እንየውንስለሁኔታው ጠይቀናቸው ወጣቶቹ መንገድሳይዘጉ እንደፈለጉ ተንቀሳቅሰው መሸጥእንደሚችሉና ማንም ሊወርስባቸው
እንደማይችል በመግለፅ ስለመወረሱምየሚያውቁት መረጃ እንደሌለ አስታውቀዋል፡፡
የአካባቢው የብአዴን/ኢህአዴግ ድርጅትጉዳይ ኃላፊ የሆኑት አቶ አያናንየወጣቶቹን ንብረት እንዲወረስ እንዳደረጉብንጠይቃቸውም ለፍኖተ ነፃነት ምላሽለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡ የመርጃው ምንጭ ሳልሳዊ ሚኒሊክ ብሎግ

No comments:

Post a Comment